# am/Amharic.xml.gz
# lv/Latvian-NT.xml.gz


(src)="b.MAT.1.1.1"> የዳዊት ልጅ የአብርሃም ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ መጽሐፍ ።
(trg)="b.MAT.1.1.1"> Jēzus Kristus , Dāvida dēla , Ābrahama dēla , cilts grāmata .

(src)="b.MAT.1.2.1"> አብርሃም ይስሐቅን ወለደ ፤ ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ ፤ ያዕቆብም ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.2.1"> Ābrahams dzemdināja Īzāku .
(trg)="b.MAT.1.2.2"> Un Īzāks dzemdināja Jēkabu .
(trg)="b.MAT.1.2.3"> Jēkabs dzemdināja Jūdu un viņa brāļus .

(src)="b.MAT.1.3.1"> ይሁዳም ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ ፤ ፋሬስም ኤስሮምን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.3.1"> Jūda dzemdināja Faresu un Zāru no Tamāras ; Faress dzemdināja Esronu ; Esrons dzemdināja Aramu ;

(src)="b.MAT.1.4.1"> ኤስሮምም አራምን ወለደ ፤ አራምም አሚናዳብን ወለደ ፤ አሚናዳብም ነአሶንን ወለደ ፤ ነአሶንም ሰልሞንን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.4.1"> Arams dzemdināja Aminadabu ; un Aminadabs dzemdināja Nāsonu ; Nāsons dzemdināja Salmonu ;

(src)="b.MAT.1.5.1"> ሰልሞንም ከራኬብ ቦኤዝን ወለደ ፤ ቦኤዝም ከሩት ኢዮቤድን ወለደ ፤ ኢዮቤድም እሴይን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.5.1"> Salmons dzemdināja Boozu no Rahabas ; Boozs dzemdināja Obedu no Rutes ; Obeds dzemdināja Jesi ; Jese dzemdināja ķēniņu Dāvidu ;

(src)="b.MAT.1.6.1"> እሴይም ንጉሥ ዳዊትን ወለደ ።
(trg)="b.MAT.1.6.1"> Ķēniņš Dāvids dzemdināja Salomonu no tās , kas bija Ūrija ;

(src)="b.MAT.1.7.1"> ሰሎሞንም ሮብዓምን ወለደ ፤ ሮብዓምም አቢያን ወለደ ፤ አቢያም አሣፍን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.7.1"> Salomons dzemdināja Roboamu ; Roboams dzemdināja Abiju ; Abijs dzemdināja Azu ;

(src)="b.MAT.1.8.1"> አሣፍም ኢዮሣፍጥን ወለደ ፤ ኢዮሣፍጥም ኢዮራምን ወለደ ፤ ኢዮራምም ዖዝያንን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.8.1"> Azs dzemdināja Jozafatu ; Jozafats dzemdināja Joramu ; Jorams dzemdināja Oziju ;

(src)="b.MAT.1.9.1"> ዖዝያንም ኢዮአታምን ወለደ ፤ ኢዮአታምም አካዝን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.9.1"> Ozijs dzemdināja Joatamu ; Joatams dzemdināja Ahazu ; Ahazs dzemdināja Ezehiju ;

(src)="b.MAT.1.10.1"> አካዝም ሕዝቅያስን ወለደ ፤ ሕዝቅያስም ምናሴን ወለደ ፤ ምናሴም አሞፅን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.10.1"> Un Ezehijs dzemdināja Manasu ; Manass dzemdināja Amonu ; Amons dzemdināja Josiju ;

(src)="b.MAT.1.11.1"> አሞፅም ኢዮስያስን ወለደ ፤ ኢዮስያስም በባቢሎን ምርኮ ጊዜ ኢኮንያንንና ወንድሞቹን ወለደ ።
(trg)="b.MAT.1.11.1"> Josijs dzemdināja Jehoniju un viņa brāļus Babilonas verdzībā .

(src)="b.MAT.1.12.1"> ከባቢሎንም ምርኮ በኋላ ኢኮንያን ሰላትያልን ወለደ ፤ ሰላትያልም ዘሩባቤልን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.12.1"> Pēc Babilonas verdzības Jehonijs dzemdināja Salatiēlu ; Salatiēls dzemdināja Zorobabelu ;

(src)="b.MAT.1.13.1"> ዘሩባቤልም አብዩድን ወለደ ፤ አብዩድም ኤልያቄምን ወለደ ፤ ኤልያቄምም አዛርን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.13.1"> Zorobabels dzemdināja Abiudu ; Abiuds dzemdināja Eliakimu ; Eliakims dzemdināja Azoru ;

(src)="b.MAT.1.14.1"> አዛርም ሳዶቅን ወለደ ፤ ሳዶቅም አኪምን ወለደ ፤ አኪምም ኤልዩድን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.14.1"> Azors dzemdināja Sadoku ; Sadoks dzemdināja Ahimu ; un Ahims dzemdināja Eliudu ;

(src)="b.MAT.1.15.1"> ኤልዩድም አልዓዛርን ወለደ ፤ አልዓዛርም ማታንን ወለደ ፤ ማታንም ያዕቆብን ወለደ ፤
(trg)="b.MAT.1.15.1"> Un Eliuds dzemdināja Eleazaru ; un Eleazars dzemdināja Matanu ; un Matans dzemdināja Jēkabu ;

(src)="b.MAT.1.16.1"> ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን እጮኛ ዮሴፍን ወለደ ።
(trg)="b.MAT.1.16.1"> Bet Jēkabs dzemdināja Jāzepu , Marijas vīru , no kuras dzimis Jēzus , kas top saukts Kristus .

(src)="b.MAT.1.17.1"> እንግዲህ ትውልድ ሁሉ ከአብርሃም እስከ ዳዊት አሥራ አራት ትውልድ ፥ ከዳዊትም እስከ ባቢሎን ምርኮ አሥራ አራት ትውልድ ፥ ከባቢሎንም ምርኮ እስከ ክርስቶስ አሥራ አራት ትውልድ ነው ።
(trg)="b.MAT.1.17.1"> Visas paaudzes tātad no Ābrahama līdz Dāvidam ir četrpadsmit paaudzes ; un no Dāvida līdz Babilonas verdzībai ir četrpadsmit paaudzes ; un no Babilonas verdzības līdz Kristum četrpadsmit paaudzes .

(src)="b.MAT.1.18.1"> የኢየሱስ ክርስቶስም ልደት እንዲህ ነበረ ። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች ።
(trg)="b.MAT.1.18.1"> Bet ar Kristus dzimšanu bija tā : kad Viņa māte Marija tika saderināta ar Jāzepu , iekams viņi sagāja kopā , izrādījās , ka viņa savās miesās ieņēmusi no Svētā Gara .

(src)="b.MAT.1.19.1"> እጮኛዋ ዮሴፍም ጻድቅ ሆኖ ሊገልጣት ስላልወደደ በስውር ሊተዋት አሰበ ።
(trg)="b.MAT.1.19.1"> Bet Jāzeps , viņas vīrs , būdams taisnīgs un negribēdams viņai neslavu celt , gribēja viņu slepeni atstāt .

(src)="b.MAT.1.20.1"> እርሱ ግን ይህን ሲያስብ ፥ እነሆ የጌታ መልአክ በሕልም ታየው ፥ እንዲህም አለ ። የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ ፥ ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና እጮኛህን ማርያምን ለመውሰድ አትፍራ ።
(trg)="b.MAT.1.20.1"> Bet kamēr viņš par to domāja , lūk , Kunga eņģelis parādījās viņam sapnī , sacīdams : Jāzep , Dāvida dēls , nebīsties pieņemt savu sievu Mariju , jo kas viņā iedzimis , ir no Svētā Gara .

(src)="b.MAT.1.21.1"> ልጅም ትወልዳለች ፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ ።
(trg)="b.MAT.1.21.1"> Viņa dzemdēs Dēlu , un tu nosauksi Viņu vārdā Jēzus , jo Viņš atpestīs savu tautu no tās grēkiem .

(src)="b.MAT.1.22.1"> በነቢይ ከጌታ ዘንድ ።
(trg)="b.MAT.1.22.1"> Bet tas viss ir noticis , lai piepildītos , ko Kungs runājis caur pravieti , kas saka :

(src)="b.MAT.1.23.1"> እነሆ ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች ፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል ፥ ትርጓሜውም ። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው ።
(trg)="b.MAT.1.23.1"> Lūk , jaunava ieņems savās miesās un dzemdēs Dēlu , un nosauks Viņu vārdā Emanuēls , kas ir tulkots : Dievs ar mums .

(src)="b.MAT.1.24.1"> ዮሴፍም ከእንቅልፉ ነቅቶ የጌታ መልአክ እንዳዘዘው አደረገ ፤ እጮኛውንም ወሰደ ፤
(trg)="b.MAT.1.24.1"> Bet Jāzeps , uzmodies no miega , darīja tā , kā Kunga eņģelis bija viņam pavēlējis , un pieņēma savu sievu .

(src)="b.MAT.1.25.1"> የበኩር ልጅዋንም እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም ፤ ስሙንም ኢየሱስ አለው ።
(trg)="b.MAT.1.25.1"> Un viņš to neatzina , kamēr viņa dzemdēja savu pirmdzimto Dēlu , nosaucot Viņu vārdā Jēzus .

(src)="b.MAT.2.1.1"> ኢየሱስም በይሁዳ ቤተ ልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ ፥ እነሆ ፥ ሰብአ ሰገል ። የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው ? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና እያሉ ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ ።
(trg)="b.MAT.2.1.1"> Kad Jēzus ķēniņa Heroda laikā bija dzimis jūdu Betlēmē , gudrie no austrumiem aizgāja uz Jeruzalemi ,

(src)="b.MAT.2.3.1"> ንጉሡ ሄሮድስም ሰምቶ ደነገጠ ፥ ኢየሩሳሌምም ሁሉ ከእርሱ ጋር ፤
(trg)="b.MAT.2.3.1"> Ķēniņš Herods , izdzirdis to , izbijās , un visa Jeruzaleme līdz ar viņu .

(src)="b.MAT.2.4.1"> የካህናትንም አለቆች የሕዝቡንም ጻፎች ሁሉ ሰብስቦ ክርስቶስ ወዴት እንዲወለድ ጠየቃቸው ።
(trg)="b.MAT.2.4.1"> Un viņš , sapulcinājis visus augstos priesterus un tautas rakstu mācītājus , iztaujāja tos , kur Kristum bija jāpiedzimst .

(src)="b.MAT.2.5.1"> እነርሱም ። አንቺ ቤተ ልሔም ፥ የይሁዳ ምድር ፥ ከይሁዳ ገዢዎች ከቶ አታንሽም ፤ ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ከአንቺ ይወጣልና ተብሎ በነቢይ እንዲህ ተጽፎአልና በይሁዳ ቤተ ልሔም ነው አሉት ።
(trg)="b.MAT.2.5.1"> Un viņi tam sacīja : Jūdu Betlēmē , jo tā pravietis rakstījis :

(src)="b.MAT.2.7.1"> ከዚህ በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገልን በስውር ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከእነርሱ በጥንቃቄ ተረዳ ፥
(trg)="b.MAT.2.7.1"> Tad Herods , slepeni pieaicinājis gudros , rūpīgi iztaujāja viņus par zvaigznes laiku , kas bija parādījusies tiem .

(src)="b.MAT.2.8.1"> ወደ ቤተ ልሔምም እነርሱን ሰድዶ ። ሂዱ ፥ ስለ ሕፃኑ በጥንቃቄ መርምሩ ፤ ባገኛችሁትም ጊዜ እኔ ደግሞ መጥቼ እንድሰግድለት ንገሩኝ አላቸው ።
(trg)="b.MAT.2.8.1"> Un , sūtīdams viņus uz Betlēmi , sacīja : Ejiet un rūpīgi iztaujājiet par Bērnu , un , kad jūs atradīsiet , ziņojiet man , lai arī es aizgājis pielūdzu Viņu !

(src)="b.MAT.2.9.1"> እነርሱም ንጉሡን ሰምተው ሄዱ ፤ እነሆም ፥ በምሥራቅ ያዩት ኮከብ ሕፃኑ ባለበት ላይ መጥቶ እስኪቆም ድረስ ይመራቸው ነበር ።
(trg)="b.MAT.2.9.1"> Šie , uzklausījuši ķēniņu , aizgāja .
(trg)="b.MAT.2.9.2"> Un , lūk , zvaigzne , ko viņi redzēja austrumos , gāja tiem pa priekšu , līdz atnākusi apstājās augšā , kur atradās Bērns .

(src)="b.MAT.2.10.1"> ኮከቡንም ባዩ ጊዜ በታላቅ ደስታ እጅግ ደስ አላቸው ።
(trg)="b.MAT.2.10.1"> Bet viņi , ieraudzījuši zvaigzni , priecājās lielā priekā .

(src)="b.MAT.2.11.1"> ወደ ቤትም ገብተው ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት ፥ ወድቀውም ሰገዱለት ፥ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን ከርቤም አቀረቡለት ።
(trg)="b.MAT.2.11.1"> Un tie , iegājuši mājā , atrada Bērnu un Viņa māti Mariju ; un Viņu , zemē nometušies , pielūdza ; un tie , atvēruši savas mantas , upurēja Viņam zeltu , vīraku un mirres .

(src)="b.MAT.2.12.1"> ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ ።
(trg)="b.MAT.2.12.1"> Un viņi , sapnī saņēmuši atbildi neatgriezties pie Heroda , pa citu ceļu aizgāja savā zemē .

(src)="b.MAT.2.13.1"> እነርሱም ከሄዱ በኋላ እነሆ ፥ የጌታ መልአክ በሕልም ለዮሴፍ ታይቶ ። ሄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይፈልገዋልና ተነሣ ፥ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ ፥ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ተቀመጥ አለው ።
(trg)="b.MAT.2.13.1"> Kad viņi bija aizgājuši , lūk , tā Kunga eņģelis parādījās Jāzepam sapnī , sacīdams : Celies un ņem Bērnu un Viņa Māti , un bēdz uz Ēģipti , un paliec tur , kamēr es tev sacīšu , jo notiks , ka Herods meklēs Bērnu nonāvēšanai !

(src)="b.MAT.2.14.1"> እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን በሌሊት ያዘና ከጌታ ዘንድ በነቢይ ። ልጄን ከግብፅ ጠራሁት የተባለው እንዲፈጸም ወደ ግብፅ ሄደ ፥ ሄሮድስም እስኪሞት ድረስ በዚያ ኖረ ።
(trg)="b.MAT.2.14.1"> Viņš , uzcēlies naktī , paņēma Bērnu un Viņa māti un aizgāja uz Ēģipti .

(src)="b.MAT.2.16.1"> ከዚህ በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገል እንደ ተሣለቁበት ባየ ጊዜ እጅግ ተቆጣና ልኮ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ የነበሩትን ፥ ሁለት ዓመት የሆናቸውን ከዚያም የሚያንሱትን ሕፃናት ሁሉ አስገደለ ።
(trg)="b.MAT.2.16.1"> Tad Herods , redzēdams , ka viņu gudrie izsmējuši , ļoti dusmojās , aizsūtīja un nogalināja visus bērnus , kuri bija Betlēmē un visā tās apkārtnē , sākot ar diviem gadiem un jaunākus , saskaņā ar laiku , kādu viņš iztaujāja gudrajiem .

(src)="b.MAT.2.17.1"> ያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ ፥ ድምፅ በራማ ተሰማ ፥ ልቅሶና ብዙ ዋይታ ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች ፥ መጽናናትም አልወደደችም ፥ የሉምና የተባለው ተፈጸመ ።
(trg)="b.MAT.2.17.1"> Tad izpildījās , ko bija teicis pravietis Jeremijs , kas sacīja :

(src)="b.MAT.2.19.1"> ሄሮድስም ከሞተ በኋላ ፥ እነሆ ፥ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ ።
(trg)="b.MAT.2.19.1"> Bet pēc Heroda nāves , lūk , Kunga eņģelis Ēģiptē parādījās Jāzepam sapnī un sacīja :

(src)="b.MAT.2.20.1"> የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ አለ ።
(trg)="b.MAT.2.20.1"> Celies un ņem Bērnu un Viņa māti , un ej uz Izraēļa zemi , jo miruši ir tie , kas tiecās pēc Bērna dvēseles .

(src)="b.MAT.2.21.1"> እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ ።
(trg)="b.MAT.2.21.1"> Un viņš piecēlās , ņēma Bērnu un Viņa māti un iegāja Izraēļa zemē .

(src)="b.MAT.2.22.1"> በአባቱም በሄሮድስ ፈንታ አርኬላዎስ በይሁዳ እንደ ነገሠ በሰማ ጊዜ ፥ ወደዚያ መሄድን ፈራ ፤ በሕልምም ተረድቶ ወደ ገሊላ አገር ሄደ ፤
(trg)="b.MAT.2.22.1"> Bet izdzirdis , ka Arhelaus valda Jūdejā , sava tēva Heroda vietā , viņš baidījās tur iet un , sapnī pamācīts , aizgāja Galilejas daļā .

(src)="b.MAT.2.23.1"> በነቢያት ። ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ፥ ናዝሬት ወደምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ ።
(trg)="b.MAT.2.23.1"> Un nogājis Viņš dzīvoja pilsētā , kura saucās Nācarete , lai izpildītos , ko pravietis bija sacījis : Viņš tiks saukts Nācarietis .

(src)="b.MAT.3.1.1"> በዚያም ወራት መጥምቁ ዮሐንስ ። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ ብሎ በይሁዳ ምድረ በዳ እየሰበከ መጣ ።
(trg)="b.MAT.3.1.1"> Tanīs dienās nāca Jānis Kristītājs , mācīdams Jūdejas tuksnesī

(src)="b.MAT.3.3.1"> በነቢዩ በኢሳይያስ ። የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮህ ሰው ድምፅ የተባለለት ይህ ነውና ።
(trg)="b.MAT.3.3.1"> Šis ir tas , par ko min pravietis Isajs , sacīdams : Saucēja balss tuksnesī : sagatavojiet Kunga ceļu , dariet taisnas Viņa tekas !

(src)="b.MAT.3.4.1"> ራሱም ዮሐንስ የግመል ጠጉር ልብስ ነበረው ፥ በወገቡም ጠፍር ይታጠቅ ነበር ፤ ምግቡም አንበጣና የበረሀ ማር ነበረ ።
(trg)="b.MAT.3.4.1"> Bet pašam Jānim bija uzvalks no kamieļu spalvām un ādas josta ap viņa gurniem ; viņa ēdiens sastāvēja no siseņiem un meža medus .

(src)="b.MAT.3.5.1"> ያን ጊዜ ኢየሩሳሌም ይሁዳም ሁሉ በዮርዳኖስም ዙሪያ ያለ አገር ሁሉ ወደ እርሱ ይወጡ ነበር ፤
(trg)="b.MAT.3.5.1"> Tad izgāja pie viņa Jeruzaleme , visa Jūdeja un viss apgabals ap Jordānu ;

(src)="b.MAT.3.6.1"> ኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር ።
(trg)="b.MAT.3.6.1"> Un viņi , atzinuši savus grēkus , pieņēma no viņa kristību Jordānā .

(src)="b.MAT.3.7.1"> ዳሩ ግን ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን ብዙዎች ወደ ጥምቀቱ ሲመጡ ባየ ጊዜ ፥ እንዲህ አላቸው ። እናንተ የእፉኝት ልጆች ፥ ከሚመጣው ቍጣ እንድትሸሹ ማን አመለከታችሁ ?
(trg)="b.MAT.3.7.1"> Bet viņš , redzēdams daudz farizeju un saduceju nākot pie kristības , sacīja tiem : čūsku izdzimums , kas norādīja jums bēgt no nākamām dusmām ?

(src)="b.MAT.3.8.1"> እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ ፤
(trg)="b.MAT.3.8.1"> Tad dariet gandarījuma cienīgus augļus !

(src)="b.MAT.3.9.1"> በልባችሁም ። አብርሃም አባት አለን እንደምትሉ አይምሰላችሁ ፤ እላችኋለሁና ። ከነዚህ ድንጋዮች ለአብርሃም ልጆች ሊያስነሣለት እግዚአብሔር ይችላል ።
(trg)="b.MAT.3.9.1"> Un nesakiet : Ābrahams ir mūsu tēvs , jo es jums saku , ka Dieva varā ir no šiem akmeņiem radīt Ābrahama dēlus ;

(src)="b.MAT.3.10.1"> አሁንስ ምሳር በዛፎች ሥር ተቀምጦአል ፤ እንግዲህ መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቈረጣል ወደ እሳትም ይጣላል ።
(trg)="b.MAT.3.10.1"> Jo cirvis jau pielikts pie koku saknēm .
(trg)="b.MAT.3.10.2"> Tātad katrs koks , kas nenes labus augļus , tiks nocirsts un ugunī iemests .

(src)="b.MAT.3.11.1"> እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል ፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል ፤
(trg)="b.MAT.3.11.1"> Jo es kristīju jūs ar ūdeni grēku nožēlošanai , bet kas pēc manis nāks , ir varenāks par mani .
(trg)="b.MAT.3.11.2"> Es neesmu cienīgs Viņam kurpes nest ; Viņš jūs kristīs Svētajā Garā un ar uguni .

(src)="b.MAT.3.12.1"> መንሹም በእጁ ነው ፥ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል ፥ ስንዴውንም በጎተራው ይከታል ፥ ገለባውን ግን በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል ።
(trg)="b.MAT.3.12.1"> Vēteklis ir Viņa rokā : un Viņš iztīrīs savu klonu , un Viņš sakrās kviešus savā šķūnī , bet pelavas sadedzinās neizdzēšamā ugunī .

(src)="b.MAT.3.13.1"> ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ ።
(trg)="b.MAT.3.13.1"> Tad atnāca Jēzus no Galilejas uz Jordānu pie Jāņa , lai tas Viņu kristītu .

(src)="b.MAT.3.14.1"> ዮሐንስ ግን ። እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን ? ብሎ ይከለክለው ነበር ።
(trg)="b.MAT.3.14.1"> Bet Jānis atturēja Viņu , sacīdams : Man jāsaņem kristību no Tevis , bet Tu nāc pie manis ?

(src)="b.MAT.3.15.1"> ኢየሱስም መልሶ ። አሁንስ ፍቀድልኝ ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው ። ያን ጊዜ ፈቀደለት ።
(trg)="b.MAT.3.15.1"> Bet Jēzus atbildēdams sacīja viņam : Lai tas tā notiek !
(trg)="b.MAT.3.15.2"> Tā taču mums pienākas izpildīt visu taisnību !
(trg)="b.MAT.3.15.3"> Tad viņš to pieļāva .

(src)="b.MAT.3.16.1"> ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ ፤ እነሆም ፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ ፤
(trg)="b.MAT.3.16.1"> Pēc kristības Jēzus tūliņ izkāpa no ūdens , un , lūk , debess atvērās , un Viņš redzēja Dieva Garu baloža veidā nolaižamies uz sevi .

(src)="b.MAT.3.17.1"> እነሆም ፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ ። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ ።
(trg)="b.MAT.3.17.1"> Un , lūk , balss no debesīm sacīja : Šis ir mans mīļais Dēls , kurš man labpatīk .

(src)="b.MAT.4.1.1"> ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው ፥
(trg)="b.MAT.4.1.1"> Tad Gars aizveda Jēzu tuksnesī , lai Viņš tiktu velna kārdināts .

(src)="b.MAT.4.2.1"> አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ ።
(trg)="b.MAT.4.2.1"> Un Viņš pēc tam , kad četrdesmit dienas un četrdesmit naktis bija gavējis , izsalka .

(src)="b.MAT.4.3.1"> ፈታኝም ቀርቦ ። የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው ።
(trg)="b.MAT.4.3.1"> Un kārdinātājs piestājās un sacīja Viņam : Ja Tu esi Dieva Dēls , saki , lai šie akmeņi kļūst maize !

(src)="b.MAT.4.4.1"> እርሱም መልሶ ። ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው ።
(trg)="b.MAT.4.4.1"> Viņš atbildēja un sacīja : Ir rakstīts : cilvēks nedzīvo no maizes vien , bet no ikviena vārda , kas iziet no Dieva mutes .

(src)="b.MAT.4.5.1"> ከዚህ በኋላ ዲያቢሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ ።
(trg)="b.MAT.4.5.1"> Tad velns ņēma Viņu sev līdz svētajā pilsētā un novietoja Viņu svētnīcas jumta galā ,

(src)="b.MAT.4.6.1"> መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው ።
(trg)="b.MAT.4.6.1"> Un sacīja Viņam : Ja Tu esi Dieva Dēls , tad meties zemē !
(trg)="b.MAT.4.6.2"> Jo ir rakstīts : Viņš saviem eņģeļiem pavēlējis par Tevi un viņi Tevi nesīs uz rokām , lai Tu kādreiz pie akmens nepiedauzītu savu kāju .

(src)="b.MAT.4.7.1"> ኢየሱስም ። ጌታን አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ደግሞ ተጽፎአል አለው ።
(trg)="b.MAT.4.7.1"> Jēzus viņam sacīja : Atkal ir rakstīts : nekārdini Dievu , savu Kungu !

(src)="b.MAT.4.8.1"> ደግሞ ዲያቢሎስ እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ ወሰደው ፥ የዓለምንም መንግሥታት ሁሉ ክብራቸውንም አሳይቶ ።
(trg)="b.MAT.4.8.1"> Atkal velns ņēma Viņu līdz ļoti augstā kalnā un rādīja Viņam visas pasaules valstis un to godību ,

(src)="b.MAT.4.9.1"> ወድቀህ ብትሰግድልኝ ይህን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው ።
(trg)="b.MAT.4.9.1"> Un sacīja Viņam : To visu es Tev došu , ja Tu , zemē mezdamies , mani pielūgsi .

(src)="b.MAT.4.10.1"> ያን ጊዜ ኢየሱስ ። ሂድ ፥ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ ስገድ እርሱንም ብቻ አምልክ ተብሎ ተጽፎአልና አለው ።
(trg)="b.MAT.4.10.1"> Tad Jēzus saka viņam : Atkāpies , sātan !
(trg)="b.MAT.4.10.2"> Jo ir rakstīts : pielūdz Dievu , savu Kungu , un Viņam vienam kalpo !

(src)="b.MAT.4.11.1"> ያን ጊዜ ዲያቢሎስ ተወው ፥ እነሆም ፥ መላእክት ቀርበው ያገለግሉት ነበር ።
(trg)="b.MAT.4.11.1"> Tad velns Viņu atstāja ; un , lūk , eņģeļi piesteidzās un kalpoja Viņam .

(src)="b.MAT.4.12.1"> ኢየሱስም ዮሐንስ አልፎ እንደ ተሰጠ በሰማ ጊዜ ወደ ገሊላ ፈቀቅ ብሎ ሄደ ።
(trg)="b.MAT.4.12.1"> Bet kad Jēzus dzirdēja , ka Jānis ir nodots , Viņš atgriezās Galilejā .

(src)="b.MAT.4.13.1"> ናዝሬትንም ትቶ በዛብሎንና በንፍታሌም አገር በባሕር አጠገብ ወደ አለችው ወደ ቅፍርናሆም መጥቶ ኖረ ።
(trg)="b.MAT.4.13.1"> Un Viņš , atstājis Nācaretes pilsētu , aizgāja dzīvot Kafarnaumā pie jūras , Zabulona un Neftalima robežās ,

(src)="b.MAT.4.14.1"> በነቢዩም በኢሳይያስ ። የዛብሎን ምድርና የንፍታሌም ምድር ፥ የባሕር መንገድ ፥ በዮርዳኖስ ማዶ ፥ የአሕዛብ ገሊላ ፤ በጨለማ የተቀመጠው ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ ፥ በሞት አገርና ጥላ ለተቀመጡትም ብርሃን ወጣላቸው
(trg)="b.MAT.4.14.1"> Lai izpildītos tas , ko pravietis Isaja sacījis :

(src)="b.MAT.4.17.1"> የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ ። ከዚያ ዘመን ጀምሮ ኢየሱስ ። መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ እያለ ይሰብክ ጀመር ።
(trg)="b.MAT.4.17.1"> No tā laika Jēzus iesāka sludināt un sacīt : Gandariet par grēkiem , jo debesvalstība atnākusi !

(src)="b.MAT.4.18.1"> በገሊላ ባሕር አጠገብ ሲመላለስም ሁለት ወንድማማች ጴጥሮስ የሚሉትን ስምዖንን ወንድሙንም እንድርያስን መረባቸውን ወደ ባሕር ሲጥሉ አየ ፥ ዓሣ አጥማጆች ነበሩና ።
(trg)="b.MAT.4.18.1"> Bet Jēzus , staigādams gar Galilejas jūru , redzēja divus brāļus : Sīmani , kas tiek saukts Pēteris , un Andreju , tā brāli , izmetam tīklus jūrā , jo viņi bija zvejnieki .

(src)="b.MAT.4.19.1"> እርሱም ። በኋላዬ ኑና ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ አላቸው ።
(trg)="b.MAT.4.19.1"> Un Viņš tiem sacīja : Sekojiet man , un es jūs padarīšu par cilvēku zvejniekiem .

(src)="b.MAT.4.20.1"> ወዲያውም መረባቸውን ትተው ተከተሉት ።
(trg)="b.MAT.4.20.1"> Un viņi tūdaļ atstāja tīklus un gāja Viņam līdz .

(src)="b.MAT.4.21.1"> ከዚያም እልፍ ብሎ ሌሎችን ሁለት ወንድማማች የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ከአባታቸው ከዘብዴዎስ ጋር በታንኳ መረባቸውን ሲያበጁ አየ ፤ ጠራቸውም ።
(trg)="b.MAT.4.21.1"> Un no turienes iedams tālāk , Viņš redzēja citus divus brāļus : Jēkabu , Zebedeja dēlu , un Jāni , tā brāli , lāpot tīklus laivā kopā ar savu tēvu Zebedeju : un Viņš tos aicināja .

(src)="b.MAT.4.22.1"> እነርሱም ወዲያው ታንኳይቱንና አባታቸውን ትተው ተከተሉት ።
(trg)="b.MAT.4.22.1"> Un viņi , atstājuši tūdaļ tīklus un tēvu , sekoja Viņam .

(src)="b.MAT.4.23.1"> ኢየሱስም በምኩራቦቻቸው እያስተማረ የመንግሥትንም ወንጌል እየሰበከ በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ በገሊላ ሁሉ ይዞር ነበር ።
(trg)="b.MAT.4.23.1"> Un Jēzus gāja pa visu Galileju , mācīdams viņu sinagogās un sludinādams valstības evaņģēliju , un dziedinādams tautu no visām slimībām un visām sērgām .

(src)="b.MAT.4.24.1"> ዝናውም ወደ ሶርያ ሁሉ ወጣ ፤ በልዩ ልዩ ደዌና ሥቃይም ተይዘው የታመሙትን ሁሉ አጋንንትም ያደሩባቸውን በጨረቃም የሚነሣባቸውን ሽባዎችንም ወደ እርሱ አመጡ ፥ ፈወሳቸውም ።
(trg)="b.MAT.4.24.1"> Un Viņa slava izpaudās visā Sīrijā ; un tie nesa pie Viņa visus neveselos , dažādu slimību un ciešanu pārņemtos un ļaunā gara apsēstos , un triekas skartos , un mēnessērdzīgos ; un Viņš tos izdziedināja .

(src)="b.MAT.4.25.1"> ከገሊላም ከአሥሩ ከተማም ከኢየሩሳሌምም ከይሁዳም ከዮርዳኖስም ማዶ ብዙ ሕዝብ ተከተሉት ።
(trg)="b.MAT.4.25.1"> Un lieli ļaužu pulki no Galilejas un Dekapoles , un Jeruzalemes , no Jūdejas un Aizjordānijas gāja Viņam līdz .

(src)="b.MAT.5.1.1"> ሕዝቡንም አይቶ ወደ ተራራ ወጣ ፤ በተቀመጠም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀረቡ ፤
(trg)="b.MAT.5.1.1"> Kad Jēzus redzēja ļaužu pulkus , Viņš uzkāpa kalnā ; un , kad Viņš bija atsēdies , mācekļi piegāja pie Viņa .

(src)="b.MAT.5.2.1"> አፉንም ከፍቶ አስተማራቸው እንዲህም አለ ።
(trg)="b.MAT.5.2.1"> Un Viņš , atdarījis savu muti , mācīja tos , sacīdams :

(src)="b.MAT.5.3.1"> በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው ፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና ።
(trg)="b.MAT.5.3.1"> Svētīgi ir garā nabadzīgie , jo viņu ir debesvalstība .

(src)="b.MAT.5.4.1"> የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው ፥ መፅናናትን ያገኛሉና ።
(trg)="b.MAT.5.4.1"> Svētīgi ir lēnprātīgie , jo viņi iemantos zemi .

(src)="b.MAT.5.5.1"> የዋሆች ብፁዓን ናቸው ፥ ምድርን ይወርሳሉና ።
(trg)="b.MAT.5.5.1"> Svētīgi ir tie , kas raud , jo viņi tiks iepriecināti .

(src)="b.MAT.5.6.1"> ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው ፥ ይጠግባሉና ።
(trg)="b.MAT.5.6.1"> Svētīgi ir tie , kas alkst un slāpst taisnības , jo viņi tiks piepildīti .

(src)="b.MAT.5.7.1"> የሚምሩ ብፁዓን ናቸው ፥ ይማራሉና ።
(trg)="b.MAT.5.7.1"> Svētīgi ir žēlsirdīgie , jo viņi tiks apžēloti .

(src)="b.MAT.5.8.1"> ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው ፥ እግዚአብሔርን ያዩታልና ።
(trg)="b.MAT.5.8.1"> Svētīgi ir sirdsšķīstie , jo viņi skatīs Dievu .

(src)="b.MAT.5.9.1"> የሚያስተራርቁ ብፁዓን ናቸው ፥ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና ።
(trg)="b.MAT.5.9.1"> Svētīgi ir miermīlīgie , jo viņi sauksies Dieva bērni .

(src)="b.MAT.5.10.1"> ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው ፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና ።
(trg)="b.MAT.5.10.1"> Svētīgi ir tie , kas cieš vajāšanu taisnības dēļ , jo viņu ir debesvalstība .

(src)="b.MAT.5.11.1"> ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ ።
(trg)="b.MAT.5.11.1"> Svētīgi esat jūs , ja jūs manis dēļ lamās un vajās , un visu ļaunu netaisni par jums runās .

(src)="b.MAT.5.12.1"> ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ ፥ ሐሴትም አድርጉ ፤ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና ።
(trg)="b.MAT.5.12.1"> Priecājieties un līksmojieties , jo jūsu alga ir liela debesīs !
(trg)="b.MAT.5.12.2"> Tā viņi ir vajājuši praviešus , kas dzīvoja pirms jums .

(src)="b.MAT.5.13.1"> እናንተ የምድር ጨው ናችሁ ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል ? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም ።
(trg)="b.MAT.5.13.1"> Jūs esat zemes sāls .
(trg)="b.MAT.5.13.2"> Bet ja sāls zaudē savas spējas , ar ko tad sālīs ?
(trg)="b.MAT.5.13.3"> Tā neder vairs nekam , tikai izmešanai ārā , lai cilvēki to samītu .

(src)="b.MAT.5.14.1"> እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም ።
(trg)="b.MAT.5.14.1"> Jūs esat pasaules gaisma .
(trg)="b.MAT.5.14.2"> Pilsēta , kas celta kalnā , nav paslēpjama .

(src)="b.MAT.5.15.1"> መብራትንም አብርተው ከዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያኖሩታል በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል ።
(trg)="b.MAT.5.15.1"> Tāpat , iededzinājis sveci , neviens neliek to zem pūra , bet svečturī , lai tā dotu gaismu visiem , kas atrodas mājā .

(src)="b.MAT.5.16.1"> መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ ።
(trg)="b.MAT.5.16.1"> Tā lai jūsu gaisma spīd cilvēkiem : lai viņi redz jūsu labos darbus un godā jūsu Tēvu , kas ir debesīs .

(src)="b.MAT.5.17.1"> እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ ፤ ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም ።
(trg)="b.MAT.5.17.1"> Nedomājiet , ka es atnācu atcelt baušļus un praviešus : es neatnācu atcelt , bet izpildīt .