# am/Amharic.xml.gz
# lt/Lithuanian.xml.gz


(src)="b.GEN.1.1.1"> በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ ።
(trg)="b.GEN.1.1.1"> Pradžioje Dievas sutvėrė dangų ir žemę .

(src)="b.GEN.1.2.1"> ምድርም ባዶ ነበረች ፥ አንዳችም አልነበረባትም ፤ ጨለማም በጥልቁ ላይ ነበረ ፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በውኃ ላይ ሰፍፎ ነበር ።
(trg)="b.GEN.1.2.1"> Žemė buvo be pavidalo ir tuščia , tamsa gaubė gelmes , ir Dievo Dvasia sklandė virš vandenų .

(src)="b.GEN.1.3.1"> እግዚአብሔርም ። ብርሃን ይሁን ኣለ ፤ ብርሃንም ሆነ ።
(trg)="b.GEN.1.3.1"> Dievas tarė : “ Teatsiranda šviesa ! ”
(trg)="b.GEN.1.3.2"> Ir atsirado šviesa .

(src)="b.GEN.1.4.1"> እግዚአብሔርም ብርሃኑ መልካም እንደ ሆነ አየ ፤ እግዚብሔርም ብርሃንንና ጨለማን ለየ ።
(trg)="b.GEN.1.4.1"> Dievas matė šviesą ir , kad tai buvo gerai , ir Dievas atskyrė šviesą nuo tamsos .

(src)="b.GEN.1.5.1"> እግዚአብሔርም ብርሃኑን ቀን ብሎ ጠራው ፥ ጨለማውንም ሌሊት አለው ። ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ ፥ አንድ ቀን ።
(trg)="b.GEN.1.5.1"> Dievas pavadino šviesą diena , o tamsą naktimi .
(trg)="b.GEN.1.5.2"> Tai buvo vakaras ir rytas ­ pirmoji diena .

(src)="b.GEN.1.6.1"> እግዚአብሔርም ። በውኆች መካከል ጠፈር ይሁን ፥ በውኃና በውኃ መካከልም ይክፈል አለ ።
(trg)="b.GEN.1.6.1"> Dievas tarė : “ Teatsiranda tvirtuma tarp vandenų , ir ji teatskiria vandenis nuo vandenų ! ”

(src)="b.GEN.1.7.1"> እግዚአብሔርም ጠፈርን አደረገ ፥ ከጠፈር በታችና ከጠፈር በላይ ያሉትንም ውኆች ለየ ፤ እንዲሁም ሆነ ።
(trg)="b.GEN.1.7.1"> Dievas padarė tvirtumą ir atskyrė vandenis , kurie buvo po tvirtuma , nuo vandenų , kurie buvo virš tvirtumos .
(trg)="b.GEN.1.7.2"> Ir taip įvyko .

(src)="b.GEN.1.8.1"> እግዚአብሔር ጠፈርን ሰማይ ብሎ ጠራው ። ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ ፥ ሁለተኛ ቀን ።
(trg)="b.GEN.1.8.1"> Dievas pavadino tvirtumą dangumi .
(trg)="b.GEN.1.8.2"> Tai buvo vakaras ir rytas ­ antroji diena .

(src)="b.GEN.1.9.1"> እግዚአብሔርም ። ከሰማይ በታች ያለው ውኃ በአንድ ስፍራ ይሰብሰብ ፥ የብሱም ይገለጥ አለ እንዲሁም ሆነ ።
(trg)="b.GEN.1.9.1"> Dievas tarė : “ Tesusirenka vandenys , kurie yra po dangumi , į vieną vietą ir tepasirodo sausuma ! ”
(trg)="b.GEN.1.9.2"> Ir taip įvyko .

(src)="b.GEN.1.10.1"> እግዚአብሔርም የብሱን ምድር ብሎ ጠራው ፤ የውኃ መከማቻውንም ባሕር አለው ፤ እግዚእብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ ።
(trg)="b.GEN.1.10.1"> Dievas pavadino sausumą žeme , o vandenų samplūdį ­ jūromis .
(trg)="b.GEN.1.10.2"> Ir Dievas matė , kad tai buvo gerai .

(src)="b.GEN.1.11.1"> እግዚአብሔርም ። ምድር ዘርን የሚሰጥ ሣርንና ቡቃያን በምድርም ላይ እንደ ወገኑ ዘሩ ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን ታብቅል አለ ፤ እንዲሁም ሆነ ።
(trg)="b.GEN.1.11.1"> Dievas tarė : “ Tegul žemė išaugina žolę , augalus , duodančius sėklą , ir vaismedžius , nešančius vaisių pagal jų rūšį , kuriuose yra jų sėkla ! ”
(trg)="b.GEN.1.11.2"> Ir taip įvyko .

(src)="b.GEN.1.12.1"> ምድርም ዘርን የሚሰጥ ሣርንና ቡቃያን እንደ ወገኑ ዘሩም ያለበትን ፍሬን የሚያፈራ ዛፍን እንደ ወገኑ አበቀለች ። እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ ።
(trg)="b.GEN.1.12.1"> Žemė išaugino žolę , augalus , duodančius sėklą pagal jų rūšį , ir medžius , nešančius vaisius pagal jų rūšį , kuriuose yra jų sėkla .
(trg)="b.GEN.1.12.2"> Ir Dievas matė , kad tai buvo gerai .

(src)="b.GEN.1.13.1"> ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ ፥ ሦስተኛ ቀን ።
(trg)="b.GEN.1.13.1"> Tai buvo vakaras ir rytas ­ trečioji diena .

(src)="b.GEN.1.14.1"> እግዚአብሔርም አለ ። ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ ፤ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ ፤
(trg)="b.GEN.1.14.1"> Dievas tarė : “ Teatsiranda šviesos dangaus tvirtumoje dienai nuo nakties atskirti ir tebūna jos ženklai pažymėti laikus , dienas ir metus .

(src)="b.GEN.1.15.1"> በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር ብርሃናት ይሁኑ ፤ እንዲሁም ሆነ ።
(trg)="b.GEN.1.15.1"> Jos težiba dangaus tvirtumoje ir apšviečia žemę ! ”
(trg)="b.GEN.1.15.2"> Ir taip įvyko .

(src)="b.GEN.1.16.1"> እግዚአብሔርም ሁለት ታላላቆች ብርሃናትን አደረገ ፤ ትልቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን ፥ ትንሹም ብርሃን በሌሊት እንዲሰለጥን ፤ ከዋክብትንም ደግሞ አደረገ ።
(trg)="b.GEN.1.16.1"> Dievas padarė dvi dideles šviesas : didesniąją ­ dienai ir mažesniąją nakčiai valdyti , ir taip pat žvaigždes .

(src)="b.GEN.1.17.1"> እግዚአብሔርም በምድር ላይ ያበሩ ዘንድ በሰማይ ጠፈር አኖራቸው ፤
(trg)="b.GEN.1.17.1"> Dievas išdėstė jas dangaus tvirtumoje , kad šviestų žemei ,

(src)="b.GEN.1.18.1"> በቀንም በሌሊትም እንዲሠለጥኑ ፥ ብርሃንንና ጨለማንም እንዲለዩ ፤ እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ ።
(trg)="b.GEN.1.18.1"> valdytų dieną bei naktį ir atskirtų šviesą nuo tamsos .
(trg)="b.GEN.1.18.2"> Ir Dievas matė , kad tai buvo gerai .

(src)="b.GEN.1.19.1"> ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ ፥ አራተኛ ቀን ።
(trg)="b.GEN.1.19.1"> Tai buvo vakaras ir rytas ­ ketvirtoji diena .

(src)="b.GEN.1.20.1"> እግዚአብሔርም አለ ። ውኃ ሕያው ነፍስ ያላቸውን ተንቀሳቃሾች ታስገኝ ፥ ወፎችም ከምድር በላይ ከሰማይ ጠፈር በታች ይብረሩ ።
(trg)="b.GEN.1.20.1"> Dievas tarė : “ Tegul vandenys knibždėte knibžda gyvūnais ir paukščiai teskraido virš žemės , padangėse ! ”

(src)="b.GEN.1.21.1"> እግዚአብሔርም ታላላቆች አንበሪዎችን ፥ ውኃይቱ እንደ ወገኑ ያስገኘቻቸውንም ተንቀሳቃሾቹን ሕያዋን ፍጥረታት ሁሉ ፥ እንደ ወገኑ የሚበሩትንም ወፎች ሁሉ ፈጠረ ፤ እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ ።
(trg)="b.GEN.1.21.1"> Taip Dievas sutvėrė didelius jūros gyvūnus ir visus kitus gyvius , kurie atsirado iš vandens , ir visus paukščius pagal jų rūšį .
(trg)="b.GEN.1.21.2"> Ir Dievas matė , kad tai buvo gerai .

(src)="b.GEN.1.22.1"> እግዚአብሔርም እንዲህ ብሎ ባረካቸው ። ብዙ ተባዙም የባሕርንም ውኃ ሙሉአት ፤ ወፎችም በምድር ላይ ይብዙ ።
(trg)="b.GEN.1.22.1"> Dievas juos palaimino , tardamas : “ Būkite vaisingi , dauginkitės ir pripildykite vandenis jūrose , o paukščiai tepripildo žemę ! ”

(src)="b.GEN.1.23.1"> ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ ፥ አምስተኛ ቀን ።
(trg)="b.GEN.1.23.1"> Tai buvo vakaras ir rytas ­ penktoji diena .

(src)="b.GEN.1.24.1"> እግዚአብሔርም አለ ። ምድር ሕያዋን ፍጥረታትን እንደ ወገኑ ፥ እንስሳትንና ተንቀሳቃሾችን የምድር አራዊትንም እንደ ወገኑ ፥ ታውጣ ፤ እንዲሁም ሆነ ።
(trg)="b.GEN.1.24.1"> Dievas tarė : “ Tegul žemė išaugina gyvūnus pagal jų rūšį : gyvulius , roplius ir laukinius žvėris , kiekvieną pagal savo rūšį ! ”
(trg)="b.GEN.1.24.2"> Ir taip įvyko .

(src)="b.GEN.1.25.1"> እግዚአብሔር የምድር አራዊትን እንደ ወገኑ አደረገ ፥ እንስሳውንም እንደ ወገኑ ፥ የመሬት ተንቀሳቃሾችንም እንደ ወገኑ አደረገ ፤ እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ ።
(trg)="b.GEN.1.25.1"> Dievas padarė laukinius žvėris , gyvulius ir visokius roplius , kiekvieną pagal jų rūšį .
(trg)="b.GEN.1.25.2"> Ir Dievas matė , kad tai buvo gerai .

(src)="b.GEN.1.26.1"> እግዚአብሔርም አለ ። ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር ፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን ፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ ።
(trg)="b.GEN.1.26.1"> Dievas tarė : “ Padarykime žmogų pagal mūsų atvaizdą ir panašumą .
(trg)="b.GEN.1.26.2"> Jie tevaldo jūros žuvis , padangių paukščius , gyvulius ir visą žemę bei visus roplius , kurie gyvena ant žemės ! ”

(src)="b.GEN.1.27.1"> እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው ፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው ።
(trg)="b.GEN.1.27.1"> Ir Dievas sutvėrė žmogų pagal savo atvaizdą ; pagal Dievo atvaizdą sutvėrė Jis jį ; vyrą ir moterį sutvėrė Jis .

(src)="b.GEN.1.28.1"> እግዚአብሔርም ባረካቸው ፥ እንዲህም አላቸው ። ብዙ ፥ ተባዙ ፥ ምድርንም ሙሉአት ፥ ግዙአትም ፤ የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው ።
(trg)="b.GEN.1.28.1"> Dievas juos palaimino ir tarė : “ Būkite vaisingi ir dauginkitės , pripildykite žemę ir užvaldykite ją , viešpataukite jūros žuvims , padangių paukščiams ir kiekvienam gyvam padarui , kuris kruta ant žemės ! ”

(src)="b.GEN.1.29.1"> እግዚአብሔርም አለ ። እነሆ መብል ይሆናችሁ ዘንድ በምድር ፊት ሁሉ ላይ ዘሩ በእርሱ ያለውን ሐመልማል ሁሉ ፥ የዛፍን ፍሬ የሚያፈራውንና ዘር ያለውንም ዛፍ ሁሉ ሰጠኋችሁ ፤
(trg)="b.GEN.1.29.1"> Dievas tarė : “ Aš jums daviau įvairias žoles , turinčias sėklą , kurios auga žemės paviršiuje , ir visus medžius , kurių vaisius turi sėklą ; jums tebūna tai maistas .

(src)="b.GEN.1.30.1"> ለምድርም አራዊት ሁሉ ፥ ለሰማይም ወፎች ሁሉ ፥ ሕያው ነፍስ ላላቸው ለምድር ተንቀሳቃሾችም ሁሉ የሚበቅለው ሐመልማል ሁሉ መብል ይሁንላቸው ፤ እንዲሁም ሆነ ።
(trg)="b.GEN.1.30.1"> Ir visiems žemės gyvūnams , visiems padangių paukščiams ir visiems , kas kruta ant žemės , kas turi gyvybę , daviau visus žaliuojančius augalus maistui ” .
(trg)="b.GEN.1.30.2"> Ir taip įvyko .

(src)="b.GEN.1.31.1"> እግዚአብሔርም ያደረገውን ሁሉ አየ ፥ እነሆም እጅግ መልካም ነበረ ። ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ ፥ ስድስተኛ ቀን ።
(trg)="b.GEN.1.31.1"> Dievas matė visa , ką buvo padaręs , ir tai buvo labai gerai .
(trg)="b.GEN.1.31.2"> Buvo vakaras ir rytas ­ šeštoji diena .

(src)="b.GEN.2.1.1"> ሰማይና ምድር ሠራዊታቸውም ሁሉ ተፈጸሙ ።
(trg)="b.GEN.2.1.1"> Taip buvo sutvertas dangus , žemė ir visi jų pulkai .

(src)="b.GEN.2.2.1"> እግዚአብሔርም የሠራውን ሥራ በሰባተኛው ቀን ፈጸመ ፤ በሰባተኛውም ቀን ከሠራው ሥራ ሁሉ ዐረፈ ።
(trg)="b.GEN.2.2.1"> Dievas septintą dieną užbaigė savo darbus ir ilsėjosi septintą dieną po visų savo darbų , kuriuos atliko .

(src)="b.GEN.2.3.1"> እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው ቀደሰውም ፤ እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአልና ።
(trg)="b.GEN.2.3.1"> Dievas palaimino septintą dieną ir ją pašventino , nes joje ilsėjosi po visų savo darbų , kuriuos Dievas sukūrė ir padarė .

(src)="b.GEN.2.4.1"> እግዚአብሔር አምላክ ሰማይንና ምድርን ባደረገ አምላክ ሰማይንና ምድርን ቀን ፥ በተፈጠሩ ጊዜ የሰማይና የምድር ልደት ይህ ነው ።
(trg)="b.GEN.2.4.1"> Tokia yra dangaus ir žemės kilmė , kai jie buvo sukurti tą dieną , kurią Viešpats Dievas sutvėrė žemę ir dangų ,

(src)="b.GEN.2.5.1"> የሜዳ ቁጥቋጦ ሁሉ በምድር ላይ ገና አልነበረም ፤ የሜዳውም ቡቃያ ሁሉ ገና አልበቀለም ነበር ፤ እግዚአብሔር አምላክ ምድር ላይ አላዘነበም ነበርና ፥ ምድርንም የሚሠራባት ሰው አልነበረም ፤
(trg)="b.GEN.2.5.1"> ir visus lauko augalus , kurių dar nebuvo žemėje , ir visas lauko žoles , kurios dar nežėlė ; nes Viešpats Dievas nesiuntė į žemę lietaus ir nebuvo žmogaus žemei įdirbti .

(src)="b.GEN.2.6.1"> ነገር ግን ጉም ከምድር ትወጣ ነበር ፥ የምድርንም ፊት ሁሉ ታጠጣ ነበር ።
(trg)="b.GEN.2.6.1"> Migla kilo nuo žemės ir drėkino jos paviršių .

(src)="b.GEN.2.7.1"> እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው ፤ በአፍንጫውም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት ፤ ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ ።
(trg)="b.GEN.2.7.1"> Ir Viešpats Dievas padarė žmogų iš žemės dulkių ir įkvėpė į jo šnerves gyvybės kvapą .
(trg)="b.GEN.2.7.2"> Taip žmogus tapo gyva siela .

(src)="b.GEN.2.8.1"> እግዚአብሔር አምላክም በምሥራቅ በዔድን ገነትን ተከለ የፈጠረውንም ሰው ከዚያው አኖረው ።
(trg)="b.GEN.2.8.1"> Viešpats Dievas sukūrė sodą Edene rytuose ir ten apgyvendino žmogų , kurį buvo sutvėręs .

(src)="b.GEN.2.9.1"> እግዚአብሔር አምላክም ለማየት ደስ የሚያሰኘውን ፥ ለመብላትም መልካም የሆነውን ዛፍ ሁሉ ከምድር አበቀለ ፤ በገነትም መካከል የሕይወትን ዛፍ ፥ መልካምንና ክፉን የሚያስታውቀውንም ዛፍ አበቀለ ።
(trg)="b.GEN.2.9.1"> Viešpats Dievas išaugino iš žemės visokių medžių , gražių pasižiūrėti ir nešančių gerus vaisius maistui ; taip pat gyvybės medį sodo viduryje ir medį pažinimo gero ir blogo .

(src)="b.GEN.2.10.1"> ወንዝም ገነትን ያጠጣ ዘንድ ከዔድን ይወጣ ነበር ፤ ከዚያም ለአራት ክፍል ይከፈል ነበር ።
(trg)="b.GEN.2.10.1"> Upė tekėjo iš Edeno sodui drėkinti ; nuo ten ji šakojosi į keturias upes .

(src)="b.GEN.2.11.1"> የአንደኛው ወንዝ ስም ፊሶን ነው ፤ እርሱም ወርቅ የሚገኝበትን የኤውላጥ ምድርን ይከብባል ፤ የዚያም ምድር ወርቅ ጥሩ ነው ፤
(trg)="b.GEN.2.11.1"> Pirmosios vardas Pišonas .
(trg)="b.GEN.2.11.2"> Ji teka aplink visą Havilos šalį , kur randamas auksas .

(src)="b.GEN.2.12.1"> ከዚያም ሉልና የከበረ ድንጋይ ይገኛል ።
(trg)="b.GEN.2.12.1"> Tos šalies auksas yra geras .
(trg)="b.GEN.2.12.2"> Ten randa bdeliją ir onikso akmenį .

(src)="b.GEN.2.13.1"> የሁለተኛውም ወንዝ ስም ግዮን ነው ፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል ።
(trg)="b.GEN.2.13.1"> Antrosios upės vardas Gihonas .
(trg)="b.GEN.2.13.2"> Ji teka aplink visą Kušo šalį .

(src)="b.GEN.2.14.1"> የሦስተኛውም ወንዝ ስም ጤግሮስ ነው ፤ እርሱም በአሦር ምሥራቅ የሚሄድ ነው ።
(trg)="b.GEN.2.14.1"> Trečiosios upės vardas Tigras .
(trg)="b.GEN.2.14.2"> Ji teka į rytus nuo Asūro .
(trg)="b.GEN.2.14.3"> O ketvirtoji upė yra Eufratas .

(src)="b.GEN.2.15.1"> አራተኛውም ወንዝ ኤፍራጥስ ነው ። እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ወስዶ ያበጃትም ይጠብቃትም ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው ።
(trg)="b.GEN.2.15.1"> Ir paėmė Viešpats Dievas žmogų ir apgyvendino jį Edeno sode , kad žmogus jį įdirbtų ir prižiūrėtų .

(src)="b.GEN.2.16.1"> እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው ። ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ፤
(trg)="b.GEN.2.16.1"> Viešpats Dievas įsakė žmogui : “ Nuo kiekvieno sodo medžio tau leista valgyti ,

(src)="b.GEN.2.17.1"> ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና ።
(trg)="b.GEN.2.17.1"> bet nuo medžio pažinimo gero ir blogo nevalgyk , nes tą dieną , kurią valgysi jo vaisių , tikrai mirsi ” .

(src)="b.GEN.2.18.1"> እግዚአብሔር አምላክም አለ ። ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም ፤ የሚመቸውን ረዳት እንፍጠርለት ።
(trg)="b.GEN.2.18.1"> Viešpats Dievas tarė : “ Negerai žmogui būti vienam .
(trg)="b.GEN.2.18.2"> Aš padarysiu jam tinkamą padėjėją ” .

(src)="b.GEN.2.19.1"> እግዚአብሔር አምላክም የምድር አራዊትንና የሰማይ ወፎችን ሁሉ ከመሬት አደረገ ፤ በምን ስም እንደሚጠራቸውም ያይ ዘንድ ወደ አዳም አመጣቸው ፤ አዳምም ሕያው ነፍስ ላለው ሁሉ በስሙ እንደ ጠራው ስሙ ያው ሆነ ።
(trg)="b.GEN.2.19.1"> Viešpats Dievas , padaręs iš žemės visus žvėris bei padangių paukščius , juos atvedė prie Adomo , kad matytų , kaip jis juos pavadins ; kaip Adomas pavadino kiekvieną gyvą padarą , toks ir yra jo vardas .

(src)="b.GEN.2.20.1"> አዳምም ለእንስሳት ሁሉ ፥ ለሰማይ ወፎችም ሁሉ ፥ ለምድር አራዊትም ሁሉ ስም አወጣላቸው ፤ ነገር ግን ለአዳም እንደ እርሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር ።
(trg)="b.GEN.2.20.1"> Adomas davė vardus visiems gyvuliams , padangių paukščiams ir visiems lauko žvėrims , tačiau tarp jų neatsirado padėjėjo , tinkamo žmogui .

(src)="b.GEN.2.21.1"> እግዚአብሔር አምላክም በአዳም ከባድ እንቅልፍን ጣለበት ፥ አንቀላፋም ፤ ከጎኑም አንዲት አጥንትን ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ዘጋው ።
(trg)="b.GEN.2.21.1"> Tada Viešpats Dievas giliai užmigdė Adomą , išėmė vieną jo šonkaulių ir tą vietą užpildė kūnu .

(src)="b.GEN.2.22.1"> እግዚአብሔር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት ፤ ወደ አዳምም አመጣት ።
(trg)="b.GEN.2.22.1"> Po to Viešpats Dievas iš šonkaulio , kurį išėmė iš žmogaus , padarė moterį ir ją atvedė pas žmogų .

(src)="b.GEN.2.23.1"> አዳምም አለ ። ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት ፥ ሥጋም ከሥጋዬ ናት ፤ እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል ።
(trg)="b.GEN.2.23.1"> Tada Adomas tarė : “ Štai kaulas iš mano kaulų ir kūnas iš mano kūno !
(trg)="b.GEN.2.23.2"> Šita bus vadinama moterimi , nes iš vyro ji paimta ” .

(src)="b.GEN.2.24.1"> ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ፥ በሚስቱም ይጣበቃል ፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ ።
(trg)="b.GEN.2.24.1"> Todėl vyras paliks savo tėvą bei motiną ir susijungs su savo žmona ; ir juodu taps vienu kūnu .

(src)="b.GEN.2.25.1"> አዳምና ሚስቱ ሁለቱም ዕራቁታቸውን ነበሩ ፥ አይተፋፈሩም ነበር ።
(trg)="b.GEN.2.25.1"> Jie abu ­ žmogus ir jo žmona ­ buvo nuogi , tačiau nesigėdijo .

(src)="b.GEN.3.1.1"> እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ ነበረ ። ሴቲቱንም ። በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን ? አላት ።
(trg)="b.GEN.3.1.1"> Gyvatė buvo gudresnė už visus žemės gyvūnus , kuriuos Viešpats Dievas sutvėrė .
(trg)="b.GEN.3.1.2"> Ji tarė moteriai : “ Ar tikrai Dievas pasakė : ‘ Nevalgykite nuo visų sodo medžių ’ ? ”

(src)="b.GEN.3.2.1"> ሴቲቱም ለእባቡ አለችው ። በገነት ካለው ከዛፍ ፍሬ እንበላለን ፤
(trg)="b.GEN.3.2.1"> Moteris atsakė gyvatei : “ Mums leista valgyti sodo medžių vaisius ,

(src)="b.GEN.3.3.1"> ነገር ግን በገነት መካከል ካለው ከዛፉ ፍሬ ፥ እግዚአብሔር አለ ። እንዳትሞቱ ከእርሱ አትብሉ አትንኩትም ።
(trg)="b.GEN.3.3.1"> išskyrus vaisius medžio , kuris yra sodo viduryje .
(trg)="b.GEN.3.3.2"> Dievas įsakė : ‘ Nevalgykite nuo jo ir nelieskite jo , kad nemirtumėte ’ ” .

(src)="b.GEN.3.4.1"> እባብም ለሴቲቱ አላት ። ሞትን አትሞቱም ፤
(trg)="b.GEN.3.4.1"> Gyvatė atsakė : “ Nemirsite !

(src)="b.GEN.3.5.1"> ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ ።
(trg)="b.GEN.3.5.1"> Dievas žino , kad tą dieną , kurią valgysite nuo jo , atsivers jūsų akys ir jūs tapsite kaip dievai , pažindami gera ir bloga ” .

(src)="b.GEN.3.6.1"> ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች ፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች ፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ ።
(trg)="b.GEN.3.6.1"> Kai moteris pamatė , kad medžio vaisiai yra tinkami maistui , patrauklūs akims ir , vieną suvalgius , galima įsigyti išminties , ji paėmė jo vaisių , pati valgė ir davė savo vyrui , ir jis valgė .

(src)="b.GEN.3.7.1"> የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ ፥ እነርሱም ዕራቁታቸውን እንደ ሆኑ አወቁ ፤ የበለስንም ቅጠሎች ሰፍተው ለእነርሱ ለራሳቸው ግልድም አደረጉ ።
(trg)="b.GEN.3.7.1"> Tada atsivėrė abiejų akys ir jie suprato esą nuogi ; juodu supynė figmedžio lapus ir pasidarė prijuostes .

(src)="b.GEN.3.8.1"> እነርሱም ቀኑ በመሸ ጊዜ የእግዚአብሔርን የአምላክን ድምፅ ከገነት ውስጥ ሲመላለስ ሰሙ ፤ አዳምና ሚስቱም ከእግዚአብሔር ከአምላክ ፊት በገነት ዛፎች መካከል ተሸሸጉ ።
(trg)="b.GEN.3.8.1"> Dienai atvėsus , išgirdę Viešpaties Dievo , vaikščiojančio sode , balsą , Adomas ir jo žmona pasislėpė nuo Viešpaties Dievo veido tarp sodo medžių .

(src)="b.GEN.3.9.1"> እግዚአብሔር አምላክም አዳምን ጠርቶ ። ወዴት ነህ ? አለው ።
(trg)="b.GEN.3.9.1"> Viešpats Dievas pašaukė Adomą : “ Kur tu esi ? ”

(src)="b.GEN.3.10.1"> እርሱም አለ ። በገነት ድምፅህን ሰማሁ ፤ ዕራቁቴንም ስለ ሆንሁ ፈራሁ ፥ ተሸሸግሁም ።
(trg)="b.GEN.3.10.1"> O tas atsiliepė : “ Išgirdau Tavo balsą ir , išsigandęs , kad esu nuogas , pasislėpiau ” .

(src)="b.GEN.3.11.1"> እግዚአብሔርም አለው ። ዕራቁትህን እንደ ሆንህ ማን ነገረህ ? ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍ በውኑ በላህን ?
(trg)="b.GEN.3.11.1"> Dievas tarė : “ Kas tau pasakė , kad tu nuogas ?
(trg)="b.GEN.3.11.2"> Gal valgei nuo medžio , nuo kurio tau įsakiau nevalgyti ? ”

(src)="b.GEN.3.12.1"> አዳምም አለ ። ከእኔ ጋር እንድትሆን የሰጠኸኝ ሴት እርስዋ ከዛፉ ሰጠችኝና በላሁ ።
(trg)="b.GEN.3.12.1"> Žmogus atsakė : “ Moteris , kurią Tu man davei , davė man nuo to medžio , ir aš valgiau ” .

(src)="b.GEN.3.13.1"> እግዚአብሔር አምላክም ሴቲቱን ። ይህ ያደረግሽው ምንድር ነው ? አላት ። ሴቲቱም አለች ። እባብ አሳተኝና በላሁ ።
(trg)="b.GEN.3.13.1"> Tada Viešpats Dievas tarė moteriai : “ Kodėl tu taip padarei ? ”
(trg)="b.GEN.3.13.2"> Moteris atsakė : “ Gyvatė mane apgavo , ir aš valgiau ” .

(src)="b.GEN.3.14.1"> እግዚአብሔር አምላክም እባቡን አለው ። ይህን ስላደረግህ ከእንስሳት ከምድር አራዊትም ሁሉ ተለይተህ አንተ የተረገምህ ትሆናለህ ፤ በሆድህም ትሄዳለህ ፥ አፈርንም በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ትበላለህ ።
(trg)="b.GEN.3.14.1"> Tada Viešpats Dievas tarė gyvatei : “ Kadangi taip padarei , esi prakeikta tarp visų gyvulių ir laukinių žvėrių .
(trg)="b.GEN.3.14.2"> Tu slinksi pilvu ir dulkes ėsi per visą savo gyvenimą !

(src)="b.GEN.3.15.1"> በአንተና በሴቲቱ መካከል ፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል ፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ ።
(trg)="b.GEN.3.15.1"> Aš sukelsiu priešiškumą tarp tavęs ir moters , tarp tavo sėklos ir moters sėklos .
(trg)="b.GEN.3.15.2"> Ji sutrins tau galvą , o tu gelsi jai į kulnį ” .

(src)="b.GEN.3.16.1"> ለሴቲቱም አለ ። በፀነስሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ ፤ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል ፥ እርሱም ገዥሽ ይሆናል ።
(trg)="b.GEN.3.16.1"> Moteriai Jis tarė : “ Aš padauginsiu tavo nėštumo vargus ir su skausmu tu gimdysi vaikus ; tave trauks prie tavo vyro , o jis tau viešpataus ” .

(src)="b.GEN.3.17.1"> አዳምንም አለው ። የሚስትህን ቃል ሰምተሃልና ፥ ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍም በልተሃልና ምድር ከአንተ የተነሣ የተረገመች ትሁን ፤ በሕይወት ዘመንህም ሁሉ በድካም ከእርስዋ ትበላለህ ፤
(trg)="b.GEN.3.17.1"> O Adomui Jis tarė : “ Kadangi tu paklausei savo žmonos ir valgei nuo medžio , apie kurį tau buvau įsakęs : ‘ Nevalgyk nuo jo ’ , ­ prakeikta bus žemė dėl tavęs !
(trg)="b.GEN.3.17.2"> Vargdamas turėsi maitintis iš jos visą savo gyvenimą .

(src)="b.GEN.3.18.1"> እሾህንና አሜከላን ታበቅልብሃለች ፤ የምድርንም ቡቃያ ትበላለህ ።
(trg)="b.GEN.3.18.1"> Erškėčius ir usnis ji augins tau , ir tu valgysi lauko augalus .

(src)="b.GEN.3.19.1"> ወደ ወጣህበት መሬት እስክትመለስ ድረስ በፊትህ ወዝ እንጀራን ትበላለህ ፤ አፈር ነህና ፥ ወደ አፈርም ትመለሳለህና ።
(trg)="b.GEN.3.19.1"> Valgysi prakaitu uždirbtą duoną , kol sugrįši į žemę , iš kurios esi paimtas .
(trg)="b.GEN.3.19.2"> Esi dulkė ir dulke vėl pavirsi ” .

(src)="b.GEN.3.20.1"> አዳምም ለሚስቱ ሔዋን ብሎ ስም አወጣ ፥ የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና ።
(trg)="b.GEN.3.20.1"> Adomas pavadino savo žmoną Ieva , nes ji tapo visų gyvųjų motina .

(src)="b.GEN.3.21.1"> እግዚአብሔር አምላክም ለአዳምና ለሚስቱ የቁርበትን ልብስ አደረገላቸው ፥ አለበሳቸውም ።
(trg)="b.GEN.3.21.1"> Viešpats Dievas padarė Adomui ir jo žmonai kailinius rūbus ir jais apvilko juos .

(src)="b.GEN.3.22.1"> እግዚአብሔር አምላክም አለ ። እነሆ አዳም መልካምንና ክፉን ለማወቅ ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ ፤ አሁንም እጁን እንዳይዘረጋ ፥ ደግሞም ከሕይወት ዛፍ ወስዶ እንዳይበላ ፥ ለዘላለምም ሕያው ሆኖ እንዳይኖር ፤
(trg)="b.GEN.3.22.1"> Tada Viešpats Dievas tarė : “ Štai žmogus tapo kaip vienas iš mūsų , pažindamas gera ir bloga ; ir dabar , kad jis , ištiesęs savo ranką , neskintų nuo gyvybės medžio ir nevalgytų , ir negyventų per amžius ” .

(src)="b.GEN.3.23.1"> ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክ ከዔድን ገነት አስወጣው ፥ የተገኘባትን መሬት ያርስ ዘንድ ።
(trg)="b.GEN.3.23.1"> Todėl Viešpats Dievas išvarė jį iš Edeno sodo dirbti žemę , iš kurios jis buvo paimtas .

(src)="b.GEN.3.24.1"> አዳምንም አስወጣው ፥ ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ ኪሩቤልንና የምትገለባበጥ የነበልባል ሰይፍን በዔድን ገነት ምሥራቅ አስቀመጠ ።
(trg)="b.GEN.3.24.1"> Išvaręs žmogų , į rytus nuo Edeno sodo Viešpats pastatė cherubus su švytruojančiu ugniniu kardu saugoti kelią prie gyvybės medžio .

(src)="b.GEN.4.1.1"> አዳምም ሚስቱን ሔዋንን አወቀ ፤ ፀነሰችም ፥ ቃየንንም ወለደች ። እርስዋም ። ወንድ ልጅ ከእግዚአብሔር አገኘሁ አለች ።
(trg)="b.GEN.4.1.1"> Ir Adomas pažino savo žmoną Ievą , ir ji tapo nėščia .
(trg)="b.GEN.4.1.2"> Ji pagimdė Kainą ir tarė : “ Įsigijau sūnų Viešpaties pagalba ” .

(src)="b.GEN.4.2.1"> ደግሞም ወንድሙን አቤልን ወለደች ። አቤልም በግ ጠባቂ ነበረ ፤ ቃየንም ምድርን የሚያርስ ነበረ ።
(trg)="b.GEN.4.2.1"> Ji dar pagimdė jo brolį Abelį .
(trg)="b.GEN.4.2.2"> Abelis buvo avių piemuo , o Kainas ­ žemdirbys .

(src)="b.GEN.4.3.1"> ከብዙ ቀን በኋላም ቃየን ከምድር ፍሬ ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን አቀረበ ፤
(trg)="b.GEN.4.3.1"> Kuriam laikui praėjus , Kainas aukojo Viešpačiui iš žemės vaisių .

(src)="b.GEN.4.4.1"> አቤልም ደግሞ ከበጎቹ በኵራትና ከስቡ አቀረበ ። እግዚአብሔርም ወደ አቤልና ወደ መሥዋዕቱ ተመለከተ ፤
(trg)="b.GEN.4.4.1"> Taip pat ir Abelis aukojo iš savo bandos riebiausių pirmagimių .
(trg)="b.GEN.4.4.2"> Viešpats pažvelgė į Abelį ir jo auką ,

(src)="b.GEN.4.5.1"> ወደ ቃየንና ወደ መሥዋዕቱ ግን አልተመለከተም ። ቃየንም እጅግ ተናደደ ፊቱም ጠቆረ ።
(trg)="b.GEN.4.5.1"> tačiau į Kainą ir jo auką Jis nepažvelgė .
(trg)="b.GEN.4.5.2"> Todėl Kainas labai supyko , ir jo veidas paniuro .

(src)="b.GEN.4.6.1"> እግዚአብሔርም ቃየንን አለው ። ለምን ተናደድህ ? ለምንስ ፊትህ ጠቆረ ?
(trg)="b.GEN.4.6.1"> Viešpats tarė Kainui : “ Kodėl tu supykai ir tavo veidas paniuro ?

(src)="b.GEN.4.7.1"> መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚበራ አይደለምን ? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅ ታደባለች ፤ ፈቃድዋም ወደ አንተ ነው ፥ አንተ ግን በእርስዋ ንገሥባት ።
(trg)="b.GEN.4.7.1"> Darydamas gera , argi nebūsi priimtas ?
(trg)="b.GEN.4.7.2"> O jei gera nedarai , nuodėmė tyko prie durų .
(trg)="b.GEN.4.7.3"> Ji traukia tave , tačiau tu turi viešpatauti jai ” .

(src)="b.GEN.4.8.1"> ቃየንም ወንድሙን አቤልን ። ና ወደ ሜዳ እንሂድ አለው ። በሜዳም ሳሉ ቃየን በወንድሙ በአቤል ላይ ተነሣበት ፥ ገደለውም ።
(trg)="b.GEN.4.8.1"> Kainas kalbėjo savo broliui Abeliui .
(trg)="b.GEN.4.8.2"> Jiems esant laukuose , Kainas užpuolė savo brolį Abelį ir jį užmušė .

(src)="b.GEN.4.9.1"> እግዚአብሔርም ቃየንን አለው ። ወንድምህ አቤል ወዴት ነው ? እርሱም አለ ። አላውቅም ፤ የወንድሜ ጠባቂው እኔ ነኝን ?
(trg)="b.GEN.4.9.1"> Tada Viešpats paklausė Kaino : “ Kur yra tavo brolis Abelis ? ”
(trg)="b.GEN.4.9.2"> O jis atsakė : “ Nežinau .
(trg)="b.GEN.4.9.3"> Argi aš esu savo brolio sargas ? ”

(src)="b.GEN.4.10.1"> አለውም ። ምን አደረግህ ? የወንድምህ የደሙ ድምፅ ከምድር ወደ እኔ ይጮኻል ።
(trg)="b.GEN.4.10.1"> Tada Viešpats tarė : “ Ką padarei ?
(trg)="b.GEN.4.10.2"> Tavo brolio kraujas šaukiasi manęs nuo žemės .

(src)="b.GEN.4.11.1"> አሁንም የወንድምህን ደም ከእጅህ ለመቀበል አፍዋን በከፈተች በምድር ላይ አንተ የተረገምህ ነህ ።
(trg)="b.GEN.4.11.1"> Taigi dabar esi prakeiktas ant žemės , kuri atsivėrė ir priėmė iš tavo rankos tavo brolio kraują .

(src)="b.GEN.4.12.1"> ምድርንም ባረስህ ጊዜ እንግዲህ ኃይልዋን አትሰጥህም ፤ በምድርም ላይ ኰብላይና ተቅበዝባዥ ትሆናለህ ።
(trg)="b.GEN.4.12.1"> Kai tu ją dirbsi , ji nebeduos tau derliaus .
(trg)="b.GEN.4.12.2"> Tu būsi klajūnas ir benamis žemėje ” .

(src)="b.GEN.4.13.1"> ቃየንም እግዚአብሔርን አለው ። ኃጢአቴ ልሸከማት የማልችላት ታላቅ ናት ።
(trg)="b.GEN.4.13.1"> Tada Kainas tarė Viešpačiui : “ Mano bausmė yra per didelė , kad galėčiau ją pakelti .

(src)="b.GEN.4.14.1"> እነሆ ዛሬ ከምድር ፊት አሳደድኸኝ ፤ ከፊትህም እሰወራለሁ ፤ በምድርም ላይ ኰብላይና ተቅበዝባዥ እሆናለሁ ፤ የሚያገኘኝም ሁሉ ይገድለኛል ።
(trg)="b.GEN.4.14.1"> Tu šiandien mane išvarai iš žemės .
(trg)="b.GEN.4.14.2"> Aš turėsiu slėptis nuo Tavęs ir būsiu klajūnas ir benamis žemėje .
(trg)="b.GEN.4.14.3"> Kas mane sutiks , užmuš ” .

(src)="b.GEN.4.15.1"> እግዚአብሔርም እርሱን አለው ። እንግዲህ ቃየንን የገደለ ሁሉ ሰባት እጥፍ ይበቀልበታል ። እግዚአብሔርም ቃየንን ያገኘው ሁሉ እንዳይገድለው ምልክት አደረገለት ።
(trg)="b.GEN.4.15.1"> Viešpats jam atsakė : “ Kas užmuš Kainą , tam septyneriopai bus atkeršyta ! ”
(trg)="b.GEN.4.15.2"> Viešpats paženklino Kainą žyme , kad nė vienas , sutikęs jį , jo nenužudytų .

(src)="b.GEN.4.16.1"> ቃየንም ከእግዚአብሔር ፊት ወጣ ፤ ከዔድንም ወደ ምሥራቅ በኖድ ምድር ተቀመጠ ።
(trg)="b.GEN.4.16.1"> Kainas pasitraukė iš Viešpaties akivaizdos ir apsigyveno Nodo šalyje , į rytus nuo Edeno .

(src)="b.GEN.4.17.1"> ቃየንም ሚስቱን አወቀ ፤ ፀነሰችም ፥ ሄኖሕንም ወለደች ። ከተማም ሠራ ፥ የከተማይቱንም ስም በልጁ ስም ሄኖሕ አላት ።
(trg)="b.GEN.4.17.1"> Kainas pažino savo žmoną , ji pastojo ir pagimdė Henochą .
(trg)="b.GEN.4.17.2"> Kainas pastatė miestą ir tą miestą pavadino savo sūnaus vardu ­ Henochas .

(src)="b.GEN.4.18.1"> ሄኖሕም ጋይዳድን ወለደ ፤ ጋይዳድም ሜኤልን ወለደ ፤ ሜኤልም ማቱሣኤልን ወለደ ፤ ማቱሣኤልም ላሜሕን ወለደ ።
(trg)="b.GEN.4.18.1"> Henocho sūnus buvo Iradas , Irado sūnus ­ Mehujaelis , Mehujaelio ­ Metušaelis , Metušaelio ­ Lamechas .

(src)="b.GEN.4.19.1"> ላሜሕም ለራሱ ሁለት ሚስቶችን አገባ ፤ የአንዲቱ ስም ዓዳ ፥ የሁለተኛይቱ ስም ሴላ ነበረ ።
(trg)="b.GEN.4.19.1"> Lamechas vedė dvi žmonas .
(trg)="b.GEN.4.19.2"> Pirmosios vardas buvo Ada , antrosios ­ Cila .

(src)="b.GEN.4.20.1"> ዓዳም ያባልን ወለደች ፤ እርሱም በድንኳን የሚቀመጡት የዘላኖች አባት ነበረ ።
(trg)="b.GEN.4.20.1"> Ada pagimdė Jabalą ; jis buvo tėvas tų , kurie gyvena palapinėse ir laiko gyvulius .