# am/sadiq.xml.gz
# it/piccardo.xml.gz


(src)="s1.1"> በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው ፡ ፡
(trg)="s1.1"> In nome di Allah , il Compassionevole , il Misericordioso

(src)="s1.2"> ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው ፤
(trg)="s1.2"> La lode [ appartiene ] ad Allah , Signore dei mondi

(src)="s1.3"> እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ
(trg)="s1.3"> il Compassionevole , il Misericordioso ,

(src)="s1.4"> የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው ፡ ፡
(trg)="s1.4"> Re del Giorno del Giudizio .

(src)="s1.5"> አንተን ብቻ እንግገዛለን ፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን ፡ ፡
(trg)="s1.5"> Te noi adoriamo e a Te chiediamo aiuto .

(src)="s1.6"> ቀጥተኛውን መንገድ ምራን ፡ ፡
(trg)="s1.6"> Guidaci sulla retta via ,

(src)="s1.7"> የእነዚያን በነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ( ምራን ፤ በሉ ) ፡ ፡
(trg)="s1.7"> la via di coloro che hai colmato di grazia , non di coloro che [ sono incorsi ] nella [ Tua ] ira , né degli sviati .

(src)="s2.1"> አ.ለ.መ
(trg)="s2.1"> Alif , Lâm , Mîm .

(src)="s2.2"> ይህ መጽሐፍ ( ከአላህ ለመኾኑ ) ጥርጥር የለበትም ፤ ለፈራህያን መሪ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.2"> Questo è il Libro su cui non ci sono dubbi , una guida per i timorati ,

(src)="s2.3"> ለነዚያ በሩቁ ነገር የሚያምኑ ሶላትንም ደንቡን ጠብቀው የሚሰግዱ ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚቸሩ ለኾኑት ፤
(trg)="s2.3"> coloro che credono nell' invisibile , assolvono all' orazione e donano di ciò di cui Noi li abbiamo provvisti ,

(src)="s2.4"> ለእነዚያም ወደ አንተ በተወረደውና ከአንተ በፊትም በተወረደው የሚያምኑ በመጨረሻይቱም ( ዓለም ) እነርሱ የሚያረጋግጡ ለኾኑት ( መሪ ነው ) ፡ ፡
(trg)="s2.4"> coloro che credono in ciò che è stato fatto scendere su di te e in ciò che è stato fatto scendere prima di te e che credono fermamente all' altra vita .

(src)="s2.5"> እነዚያ ከጌታቸው በመመራት ላይ ናቸው ፤ እነዚያም እነሱ ፍላጎታቸውን ያገኙ ናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.5"> Quelli seguono la guida del loro Signore ; quelli sono coloro che prospereranno .

(src)="s2.6"> እነዚያ የካዱት ( ሰዎች ) ብታስፈራራቸውም ባታስፈራራቸውም በነርሱ ላይ እኩል ነው ፤ አያምኑም ፡ ፡
(trg)="s2.6"> In verità [ per ] quelli che non credono , non fa differenza che tu li avverta oppure no : non crederanno .

(src)="s2.7"> አላህ በልቦቻቸው ላይ በመስሚያቸውም ላይ አትሞባቸዋል ፤ በዓይኖቻቸውም ላይ መሸፈኛ አልለ ፤ ለነሱም ታላቅ ቅጣት አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.7"> Allah ha posto un sigillo sui loro cuori e sulle loro orecchie e sui loro occhi c'è un velo ; avranno un castigo immenso .

(src)="s2.8"> ከሰዎችም « በአላህና በመጨረሻው ቀን አምነናል » የሚሉ አልሉ ፤ እነርሱም አማኞች አይደሉም ፡ ፡
(trg)="s2.8"> Tra gli uomini vi è chi dice : “ Crediamo in Allah e nel Giorno Ultimo !” e invece non sono credenti .

(src)="s2.9"> አላህንና እነዚያን ያመኑትን ( ሰዎች ) ያታልላሉ ፤ የማያውቁ ሲኾኑ ነፍሶቻቸውን እንጅ ሌላን አያታልሉም ፡ ፡
(trg)="s2.9"> Cercano di ingannare Allah e coloro che credono , ma non ingannano che loro stessi e non se ne accorgono .

(src)="s2.10"> በልቦቻቸው ውስጥ ( የንፍቅና ) በሽታ አለባቸው ፡ ፡ አላህም በሽታን ጨመረባቸው ፡ ፡ ለነርሱም ይዋሹ በነበሩት ምክንያት አሳማሚ ቅጣት አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.10.0"> Nei loro cuori c'è una malattia e Allah ha aggravato questa malattia .
(trg)="s2.10.1"> Avranno un castigo doloroso per la loro menzogna .

(src)="s2.11"> ለነርሱም « በምድር ላይ አታበላሹ » በተባሉ ጊዜ « እኛ አሳማሪዎች ብቻ ነን » ይላሉ ፡ ፡
(trg)="s2.11"> E quando si dice loro : “ Non spargete la corruzione sulla terra” , dicono : “ Anzi , noi siamo dei conciliatori !” .

(src)="s2.12"> ንቁ እነርሱ አጥፊዎቹ እነሱው ናቸው ፤ ግን አያውቁም ፡ ፡
(trg)="s2.12.0"> Non sono forse questi i corruttori ?
(trg)="s2.12.1"> Ma non se ne avvedono .

(src)="s2.13"> ለነሱም « ሰዎቹ እንዳመኑ እመኑ » በተባሉ ጊዜ « ቂሎቹ እንዳመኑ እናምናለን ? » ይላሉ ፡ ፡ አዋጅ ንቁ እነርሱ ቂሎቹ እነርሱው ናቸው ፤ ግን አያውቁም ፡ ፡
(trg)="s2.13.0"> E quando si dice loro : “ Credete come hanno creduto gli altri uomini” , rispondono : “ Dovremmo credere come hanno creduto gli stolti ?” .
(trg)="s2.13.1"> Non sono forse loro gli stolti ?

(src)="s2.14"> እነዚያንም ያመኑትን በተገናኙ ጊዜ « አምነናል » ይላሉ ፡ ፡ ወደ ሰይጣኖቻቸውም ባገለሉ ጊዜ « እኛ ከናንተ ጋር ነን ፤ እኛ ( በነሱ ) ተሳላቂዎች ብቻ ነን » ይላሉ ፡ ፡
(trg)="s2.14"> Quando incontrano i credenti , dicono : “ Crediamo” ; ma quando sono soli con i loro dèmoni , dicono : “ Invero siamo dei vostri ; non facciamo che burlarci di loro” .

(src)="s2.15"> አላህ በነሱ ይሳለቅባቸዋል ፤ በጥመታቸውም ውስጥ የሚዋልሉ ሲኾኑ ያዘገያቸዋል ፡ ፡
(trg)="s2.15"> Allah si burla di loro , lascia che sprofondino nella ribellione , accecati .

(src)="s2.16"> እነዚህ እነዚያ ስህተትን በቅንነት የገዙ ናቸው ፡ ፡ ንግዳቸውም አላተረፈችም ፤ ቀጥተኞችም አልኾኑም ፡ ፡
(trg)="s2.16.0"> Sono quelli che hanno scambiato la retta Guida con la perdizione .
(trg)="s2.16.1"> Il loro è un commercio senza utile e non sono ben guidati .

(src)="s2.17"> ( በንፍቅና ) ምሳሌያቸው እንደዚያ እሳትን እንዳነደደ ሰው በዙሪያው ያለውን ሁሉ ባበራች ጊዜም አላህ ብርሃናቸውን እንደወሰደባቸው በጨለማዎችም ውስጥ የማያዩ ኾነው እንደተዋቸው ( ሰዎች ) ብጤ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.17"> Assomigliano a chi accende un fuoco ; poi , quando il fuoco ha illuminato i suoi dintorni , Allah sottrae loro la luce e li abbandona nelle tenebre in cui non vedono nulla .

(src)="s2.18"> ( እነሱ ) ደንቆሮዎች ፣ ዲዳዎች ፣ ዕውሮች ናቸው ፤ ስለዚህ እነርሱ አይመለሱም ፡ ፡
(trg)="s2.18"> Sordi , muti , ciechi , non possono ritornare .

(src)="s2.19"> ወይም ( ምሳሌያቸው ) ከሰማይ እንደ ወረደ ዝናም ( ባለቤቶች ) ነው ፤ በርሱ ( በደመናው ) ውስጥ ጨለማዎች ፣ ነጎድጓድም ፣ ብልጭታም ያሉበት ሲኾን ከመብረቆቹ ሞትን ለመፍራት ጣቶቻቸውን በጆሮቻቸው ውስጥ እንደሚያደርጉ ብጤ ነው ፡ ፡ አላህም ከሓዲዎችን ከባቢ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.19.0"> [ O come ] una nuvola di pioggia nel cielo , gonfia di tenebre , di tuoni e di fulmini : mettono le loro dita nelle orecchie temendo la morte a causa dei fulmini .
(trg)="s2.19.1"> E Allah accerchia i miscredenti .

(src)="s2.20"> ብልጭታው ዓይኖቻቸውን ሊነጥቅ ይቀርባል ፡ ፡ ለነርሱ ባበራላቸው ቁጥር በርሱ ውስጥ ይኼዳሉ ፡ ፡ በነሱም ላይ ባጨለመ ጊዜ ይቆማሉ ፡ ፡ አላህም በሻ ኖሮ መስሚያቸውንና ማያዎቻቸውን በወሰደ ነበር ፤ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነውና ፡ ፡
(trg)="s2.20.0"> Il lampo quasi li acceca : ogni volta che rischiara , procedono ; ma quando rimangono nell' oscurità si fermano .
(trg)="s2.20.1"> Se Allah avesse voluto , li avrebbe privati dell' udito e della vista .

(src)="s2.21"> እናንተ ሰዎች ሆይ ! የፈጠራችሁን እነዚያንም ከናንተ በፊት የነበሩትን ( የፈጠረውን ) ጌታችሁን ተገዙ ፤ ( ቅጣትን ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና ፡ ፡
(trg)="s2.21"> O uomini , adorate il vostro Signore Che ha creato voi e quelli che vi hanno preceduto , cosicché possiate essere timorati .

(src)="s2.22"> ( እርሱ ) ያ ለናንተ ምድርን ምንጣፍ ሰማይንም ጣራ ያደረገ ነው ፤ ከሰማይም ( ከደመና ) ውሃን ያወረደ በርሱም ከፍሬዎች ለናንተ ሲሳይን ያወጣ ነው ፡ ፡ እናንተም ( ፈጣሪነቱን ) የምታውቁ ስትኾኑ ለአላህ ባላንጣዎችን አታድርጉ ፡ ፡
(trg)="s2.22.0"> [ Egli è ] Colui Che della terra ha fatto un letto e del cielo un edificio , e che dal cielo fa scendere l' acqua con la quale produce i frutti che sono il vostro cibo .
(trg)="s2.22.1"> Non attribuite consimili ad Allah ora che sapete .

(src)="s2.23"> በባሪያችንም ላይ ካወረድነው በመጠራጠር ውስጥ ብትኾኑ ከብጤው አንዲትን ምዕራፍ አምጡ ፡ ፡ እውነተኞችም እንደኾናችሁ ከአላህ ሌላ መስካሪዎቻችሁን ጥሩ ፡ ፡
(trg)="s2.23"> E se avete qualche dubbio in merito a quello che abbiamo fatto scendere sul Nostro Servo , portate allora una sura simile a questa e chiamate altri testimoni all' infuori di Allah , se siete veritieri .

(src)="s2.24"> ( ይህንን ) ባትሠሩ ፈጽሞም አትሠሩትምና ያችን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ድንጋዮች የኾነችውን እሳት ተጠበቁ ፤ ለከሓዲዎች ተደግሳለች ፡ ፡
(trg)="s2.24"> Se non lo fate - e non lo farete - temete il Fuoco , il cui combustibile sono gli uomini e le pietre , che è stato preparato per i miscredenti .

(src)="s2.25"> እነዚያን ያመኑትንና መልካሞችንም የሠሩትን ለነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች ያሏቸው መኾኑን አብስራቸው ፡ ፡ ከርሷ ከፍሬ ( ዓይነት ) ሲሳይን በተመገቡ ቁጥር ( ፍሬዎችዋ ስለሚመሳሰሉ ) « ይህ ያ ከአሁን በፊት የተገመብነው ነው » ይላሉ ፡ ፡ እርሱንም ተመሳሳይ ኾኖ ተሰጡት ፡ ፡ ለነሱም በውስጧ ንጹህ የተደረጉ ሚስቶች አሏቸው ፡ ፡ እነሱም በውስጧ ዘውታሪዎች ናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.25.0"> E annuncia a coloro che credono e compiono il bene , che avranno i Giardini in cui scorrono i ruscelli .
(trg)="s2.25.1"> Ogni volta che sarà loro dato un frutto diranno : “ Già ci era stato concesso !” .

(src)="s2.26"> አላህ ማንኛውንም ነገር ትንኝንም ኾነ ( በትንሽነት ወይም በትልቅነት ) ከበላይዋ የኾነንም ምሳሌ ለማድረግ አያፍርም ፡ ፡ እነዚያ ያመኑትማ ፤ እርሱ ( ምሳሌው ) ከጌታቸው ( የተገኘ ) እውነት መኾኑን ያውቃሉ ፡ ፡ እነዚያም የካዱትማ « አላህ በዚህ ምንን ምሳሌ ሻ » ይላሉ ፡ ፡ በርሱ ( በምሳሌው ) ብዙዎችን ያሳስታል በርሱም ብዙዎችን ያቀናል ፡ ፡ በርሱም አመፀኞችን እንጅ ሌላን አያሳስትም ፡ ፡
(trg)="s2.26.0"> In verità , Allah non esita a prendere ad esempio un moscerino o qualsiasi altra cosa superiore .
(trg)="s2.26.1"> Coloro che credono sanno che si tratta della verità che proviene dal loro Signore ; i miscredenti invece dicono : “ Cosa vuol dire Allah con un simile esempio ?” .

(src)="s2.27"> እነዚያ የአላህን ቃል ኪዳን ከአጠበቀባቸው በኋላ የሚያፈርሱ እንዲቀጠልም በርሱ ያዘዘውን ነገር የሚቆርጡ በምድርም ላይ የሚያበላሹ እነዚያ እነርሱ ከሳሪዎቹ ናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.27.0"> coloro che rompono il patto di Allah dopo averlo accettato , spezzano ciò che Allah ha ordinato di unire e spargono la corruzione sulla terra .
(trg)="s2.27.1"> Quelli sono i perdenti .

(src)="s2.28"> ሙታን የነበራችሁ ስትኾኑ ሕያው ያደረጋችሁ ከዚያም የሚገድላችሁ ከዚያም ሕያው የሚያደርጋችሁ ሲኾን ከዚያም ወደርሱ የምትመለሱ ስትኾኑ በአላህ እንዴት ትክዳለችሁ !
(trg)="s2.28.0"> Come potete essere ingrati nei confronti di Allah , quando eravate morti ed Egli vi ha dato la vita ?
(trg)="s2.28.1"> Poi vi farà morire e vi riporterà alla vita e poi a Lui sarete ricondotti .

(src)="s2.29"> እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው ፡ ፡ ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ ፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው ፡ ፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.29.0"> Egli ha creato per voi tutto quello che c'è sulla terra .
(trg)="s2.29.1"> Poi si è rivolto al cielo e lo ha ordinato in sette cieli .

(src)="s2.30"> ( ሙሐመድ ሆይ ) ጌታህ ለመላእክት ፡ - « እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ ፤ » ባለ ጊዜ ( የኾነውን አስታውስ ፤ እነርሱም ) « እኛ ከማመስገን ጋር የምናጠራህ ላንተም የምንቀድስ ስንኾን በርሷ ውስጥ የሚያጠፋንና ደሞችንም የሚያፈስን ታደርጋለህን ? » አሉ ፡ ፡ ( አላህ ) « እኔ የማታውቁትን ነገር አውቃለሁ » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.30.0"> E quando il tuo Signore disse agli Angeli : “ Porrò un vicario sulla terra” , essi dissero : “ Metterai su di essa qualcuno che vi spargerà la corruzione e vi verserà il sangue , mentre noi Ti glorifichiamo lodandoTi e Ti santifichiamo ?” .
(trg)="s2.30.1"> Egli disse : “ In verità , Io conosco quello che voi non conoscete ...” .

(src)="s2.31"> አደምንም ስሞችን ሁሏንም አስተማረው ፡ ፡ ከዚያም በመላእክት ላይ ( ተጠሪዎቹን ) አቀረባቸው ፡ ፡ « እውነተኞችም እንደኾናችሁ የነዚህን ( ተጠሪዎች ) ስሞች ንገሩኝ » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.31"> Ed insegnò ad Adamo i nomi di tutte le cose , quindi le presentò agli Angeli e disse : “ Ditemi i loro nomi , se siete veritieri” .

(src)="s2.32"> « ጥራት ይገባህ ፤ ከአስተማርከን ነገር በስተቀር ለኛ ዕውቀት የለንም ፡ ፡ አንተ ዐዋቂው ጥበበኛው አንተ ብቻ ነህና » ( አሉ ) ፡ ፡
(trg)="s2.32.0"> Essi dissero : “ Gloria a Te .
(trg)="s2.32.1"> Non conosciamo se non quello che Tu ci hai insegnato : in verità Tu sei il Saggio , il Sapiente” .

(src)="s2.33"> ፡ - « አደም ሆይ ስሞቻቸውን ንገራቸው » አለው ፡ ፡ ስሞቻቸውን በነገራቸውም ጊዜ « እኔ የሰማያትንና የምድርን ሩቅ ምስጢር ዐውቃለሁ ፤ የምትገልጹትንና ያንንም ትደብቁት የነበራችሁትን ዐውቃለሁ አላልኳችሁምን ? » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.33.0"> Disse : “ O Adamo , informali sui nomi di tutte [ le cose ]” .
(trg)="s2.33.1"> Dopo che li ebbe informati sui nomi , Egli disse : “ Non vi avevo forse detto che conosco il segreto dei cieli e della terra e che conosco ciò che manifestate e ciò che nascondete ?” .

(src)="s2.34"> ለመላእክትም « ለአደም ስገዱ » ባልን ጊዜ ( አስታውስ ) ፡ ፡ ሁሉም ወዲያውኑ ሰገዱ ፤ ኢብሊስ ( ዲያብሎስ ) ብቻ ሲቀር እምቢ አለ ፤ ኮራም ከከሓዲዎቹም ኾነ ፡ ፡
(trg)="s2.34"> E quando dicemmo agli Angeli : “ Prosternatevi ad Adamo” , tutti si prosternarono , eccetto Iblîs , che rifiutò per orgoglio e fu tra i miscredenti .

(src)="s2.35"> « አደም ሆይ ! አንተ ከነሚስትህ በገነት ተቀመጥ ፤ ከርሷም በፈለጋችሁት ስፍራ በሰፊው ተመገቡ ፤ ግን ይህችን ዛፍ አትቅረቡ ፤ ከበደለኞች ትኾናላችሁና » አልንም ፡ ፡
(trg)="s2.35.0"> E dicemmo : “ O Adamo , abita il Paradiso , tu e la tua sposa .
(trg)="s2.35.1"> Saziatevene ovunque a vostro piacere , ma non avvicinatevi a quest' albero , ché in tal caso sareste tra gli empi” .

(src)="s2.36"> ከርሷም ሰይጣን አዳለጣቸው በውስጡም ከነበሩበት ( ድሎት ) አወጣቸው ፡ ፡ « ከፊላችሁም ለከፊሉ ጠላት ሲኾን ውረዱ ፤ ለናንተም በምድር ላይ እስከ ጊዜ ( ሞታችሁ ) ድረስ መርጊያና መጣቀሚያ አላችሁ » አልናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.36.0"> Poi Iblîs li fece inciampare e scacciare dal luogo in cui si trovavano .
(trg)="s2.36.1"> E Noi dicemmo : “ Andatevene via , nemici gli uni degli altri .

(src)="s2.37"> አደምም ከጌታው ቃላትን ተቀበለ ፡ ፡ በርሱ ላይም ( ጌታው ጸጸትን በመቀበል ) ተመለሰለት ፤ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና ፡ ፡
(trg)="s2.37.0"> Adamo ricevette parole dal suo Signore e Allah accolse il suo [ pentimento ] .
(trg)="s2.37.1"> In verità Egli è Colui Che accetta il pentimento , il Misericordioso .

(src)="s2.38"> « ሁላችሁም ኾናችሁ ከርሷ ውረዱ ፡ ፡ ከኔም የኾነ መመሪያ ቢመጣላችሁ ወዲያውኑ መመሪያዬን የተከተለ ሰው በነሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም ፤ እነሱም አያዝኑም » አልናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.38.0"> Dicemmo : “ Andatevene via tutti [ quanti ] !
(trg)="s2.38.1"> Se mai vi giungerà una guida da parte Mia , coloro che la seguiranno non avranno nulla da temere e non saranno afflitti” .

(src)="s2.39"> እነዚያም ( በመልክተኞቻችን ) የካዱ በአንቀጾቻችንም ያስተባበሉ እነዚያ የእሳት ጓዶች ናቸው ፡ ፡ እነርሱ በውስጧ ዘውታሪዎች ናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.39"> E i miscredenti che smentiscono i Nostri segni , sono i compagni del Fuoco , in cui rimarranno per sempre .

(src)="s2.40"> የእስራኤል ልጆች ሆይ ! ያችን በናንተ ላይ የለገስኳትን ጸጋዬን አስታውሱ ፡ ፡ በቃል ኪዳኔም ሙሉ ፤ በቃል ኪዳናችሁ እሞላለሁና ፤ እኔንም ብቻ ፍሩ ፡ ፡
(trg)="s2.40.0"> O figli di Israele , ricordate i favori di cui vi ho colmati e rispettate il Mio patto e rispetterò il vostro .
(trg)="s2.40.1"> Solo Me dovete temere .

(src)="s2.41"> ከናንተ ጋር ያለውን ( መጽሐፍ ) የሚያረጋግጥ ሆኖ ባወረድኩትም ( ቁርኣን ) እመኑ ፡ ፡ በርሱም የመጀመሪያ ከሓዲ አትሁኑ ፡ ፡ በአንቀጾቼም ጥቂትን ዋጋ አትለውጡ ፡ ፡ እኔንም ብቻ ተጠንቀቁ ፡
(trg)="s2.41.0"> E credete in ciò che ho fatto scendere a conferma di quello che già era sceso su di voi e non siate i primi a rinnegarlo : non svendete i Miei segni per un prezzo vile .
(trg)="s2.41.1"> E temete soltanto Me .

(src)="s2.42"> እውነቱንም በውሸት አትቀላቅሉ ፡ ፡ እናንተም የምታውቁ ስትሆኑ እውነትን አትደብቁ ፡ ፡
(trg)="s2.42"> E non avvolgete la verità di menzogna e non nascondete la verità ora che la conoscete .

(src)="s2.43"> ሶላትንም ደንቡን ጠብቃችሁ ስገዱ ፡ ፡ ዘካንም ( ግዴታ ምጽዋትን ) ስጡ ፡ ፡ ( ለጌታችሁ ) ከአጎንባሾች ጋርም አጎንብሱ ፡ ፡
(trg)="s2.43"> E assolvete all' orazione , pagate la decima e inchinatevi con coloro che si inchinano .

(src)="s2.44"> እናንተ መጽሐፉን የምታነቡ ሆናችሁ ሰዎችን በበጎ ሥራ ታዛላችሁን ? ነፍሶቻችሁንም ትረሳላችሁን ? ( የሥራችሁን መጥፎነት ) አታውቁምን ?
(trg)="s2.44.0"> Ordinerete ai popoli la carità e dimenticherete voi stessi , voi che leggete il Libro ?
(trg)="s2.44.1"> Non ragionate dunque ?

(src)="s2.45"> በመታገስና በሶላትም ተረዱ ፡ ፡ እርሷም ( ሶላት ) በፈሪዎች ላይ እንጅ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት ፡ ፡
(trg)="s2.45"> Cercate aiuto nella pazienza e nell' adorazione , in verità essa è gravosa , ma non per gli umili

(src)="s2.46"> እነዚያ እነርሱ ጌታቸውን የሚገናኙ እነሱም ወደእርሱ ተመላሾች መኾናቸውን የሚያረጋግጡ በኾኑት ( ላይ እንጅ ከባድ ናት ) ፡ ፡
(trg)="s2.46"> che pensano che invero incontreranno il loro Signore e che invero torneranno a Lui .

(src)="s2.47"> የእስራኤል ልጆች ሆይ ! ያችን በናንተ ላይ የለገስኳትን ጸጋዬንና እኔም በዓለማት ላይ ያበለጥኳችሁ ( አባቶቻችሁን በጊዜያቸው ከነበሩት ዓለማት ያበለጥኩዋቸው ) መኾኔን አስታውሱ ፡ ፡
(trg)="s2.47"> O Figli di Israele , ricordate i favori di cui vi ho colmati e di come vi ho favorito sugli altri popoli del mondo .

(src)="s2.48"> ( ማንኛዋ ) ነፍስም ከ ( ሌላዋ ) ነፍስ ምንንም የማትመነዳበትን ፣ ከርሷም ምልጃን የማይቀበሉባትን ፣ ከርሷም ቤዛ የማይያዝበትን ፣ እነርሱም የማይረዱበትን ቀን ተጠንቀቁ ፡ ፡
(trg)="s2.48.0"> E temete il Giorno in cui nessun'anima potrà alcunché per un' altra , in cui non sarà accolta nessuna intercessione e nulla potrà essere compensato .
(trg)="s2.48.1"> Essi non saranno soccorsi .

(src)="s2.49"> ከፈርዖንም ቤተሰቦች ( ከጎሶቹና ከሰራዊቱ ) ብርቱን ቅጣት የሚያቀምሱዋችሁ ወንዶች ልጆቻችሁን የሚያርዱ ሴቶቻችሁንም የሚተው ሲኾኑ ባዳንናችሁ ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ) ፡ ፡ በዚሃችሁም ከጌታችሁ ታላቅ ፈተና አለበት ፡ ፡
(trg)="s2.49.0"> E [ ricordate ] quando vi abbiamo liberato dalla gente di Faraone che vi infliggeva le torture più atroci ! ...
(trg)="s2.49.1"> Sgozzavano i vostri figli e lasciavano in vita le vostre femmine .

(src)="s2.50"> በናንተም ምክንያት ባሕሩን በከፈልን ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡ ወዲያውም አዳንናችሁ ፡ ፡ የፈርዖንንም ቤተሰቦች እናንተ የምትመለከቱ ኾናችሁ አሰጠምናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.50"> E quando abbiamo diviso il mare per voi , quindi vi abbiamo tratti in salvo e abbiamo annegato la gente di Faraone , mentre voi stavate a guardare .

(src)="s2.51"> ሙሳንም አርባን ሌሊት በቀጠርነው ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ) ፡ ፡ ከዚያም ከርሱ ( መኼድ ) በኋላ እናንተ በዳዮች ስትኾኑ ወይፈንን ( አምላክ አድርጋችሁ ) ያዛችሁ ፡ ፡
(trg)="s2.51"> E quando stabilimmo con Mosè [ un patto in ] quaranta notti ... e voi vi prendeste il Vitello e agiste da iniqui .

(src)="s2.52"> ከዚያም ከዚህ በኋላ እናንተ ታመሰግኑ ዘንድ ከናንተ ምሕረት አደረግን ፡ ፡
(trg)="s2.52"> Ma Noi vi perdonammo : forse ne sareste stati riconoscenti .

(src)="s2.53"> ሙሳንም መጽሐፍንና ( እውነትና ውሸትን ) መለያንም ትመሩ ዘንድ በሰጠነው ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡
(trg)="s2.53"> E quando abbiamo dato a Mosè il Libro e il Discrimine : forse sarete ben guidati !

(src)="s2.54"> ሙሳም ለሕዝቦቹ ፡ - « ሕዝቦቼ ሆይ ! እናንተ ወይፈንን ( አምላክ አድርጋችሁ ) በመያዛችሁ ነፍሶቻችሁን በደላችሁ ፡ ፡ ወደ ፈጣሪያችሁም ተመለሱ ፤ ነፍሶቻችሁንም ግደሉ ፤ ይሃችሁ በፈጣሪያችሁ ዘንድ ለናንተ በላጭ ነው » ባለ ጊዜ ( አስታውስ ) ፡ ፡ በእናንተም ላይ ጸጸትን በመቀበል ተመለሰላችሁ ፡ ፡ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና ፡ ፡
(trg)="s2.54.0"> E quando Mosè disse al suo popolo : “ O popol mio , invero vi siete fatti un grande torto prendendovi il Vitello .
(trg)="s2.54.1"> Pentitevi al vostro Creatore e datevi la morte : questa è la cosa migliore , di fronte al vostro Creatore” .

(src)="s2.55"> « ሙሳ ሆይ ! አላህን በግልጽ እስከምናይ ድረስ ላንተ በፍጹም አናምንልህም » በላችሁም ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡ እናንተም እየተመለከታችሁ መብረቅ ያዘቻችሁ ፡ ፡
(trg)="s2.55.0"> E quando diceste : “ O Mosè , noi non ti crederemo finché non avremo visto Allah in maniera evidente” .
(trg)="s2.55.1"> E la folgore vi colpì mentre stavate guardando .

(src)="s2.56"> ከዚያም ታመሰግኑ ዘንድ ከሞታችሁ በኋላ አስነሳናችሁ ፡ ፡
(trg)="s2.56"> Poi vi resuscitammo dalla morte : forse sarete riconoscenti .

(src)="s2.57"> በናንተም ላይ ደመናን አጠለልን ፡ ፡ በናተም ላይ ( እንደ ነጭ ማር ያለ ) መንናን እና ድርጭትን አወረድን ፡ ፡ ከሰጠናችሁም ጣፋጮች « ብሉ ( አልን ) ፡ ፡ » አልበደሉንምም ግን ነፍሶቻቸውን ይበድሉ ነበር ፡ ፡
(trg)="s2.57.0"> E vi coprimmo con l' ombra di una nuvola , e facemmo scendere su di voi la manna e le quaglie : “ Mangiate queste delizie di cui vi abbiamo provvisti !” .
(trg)="s2.57.1"> Non è a Noi che fecero torto , bensì a loro stessi .

(src)="s2.58"> « ይህችንም ከተማ ግቡ ፡ ፡ ከርሷም በሻችሁት ስፍራ ሰፊን ( ምግብ ) ተመገቡ ፡ ፡ በሩንም ያጎነበሳችሁ ኾናችሁ ግቡ ፤ ( ጥያቄያችን የኃጢአታችን መርገፍ ነው ) በሉም ፡ ፡ ኃጢአቶቻችሁን ለናንተ እንምራለንና ፡ ፡ በጎ ሠሪዎችንም ( ምንዳን ) እንጨምርላቸዋለን » ባልን ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡
(trg)="s2.58.0"> E quando dicemmo : “ Entrate in questa città e rifocillatevi dove volete a vostro piacimento ; ma entrate dalla porta inchinandovi e dicendo " perdono " .
(trg)="s2.58.1"> Noi perdoneremo i vostri peccati ed aumenteremo coloro che avranno operato il bene” .

(src)="s2.59"> እነዚያም የበደሉት ሰዎች ከዚያ ለነሱ ከተባሉት ሌላ ቃልን ለወጡ ፡ ፡ በነዚያም በበደሉት ላይ ያመጹ በመሆናቸው ምክንያት መቅሠፍትን አወረድንባቸው ፡ ፡
(trg)="s2.59.0"> Ma gli empi cambiarono la parola che era stata data loro .
(trg)="s2.59.1"> E facemmo scendere dal cielo un castigo sugli empi , per castigare la loro perversione .

(src)="s2.60"> ሙሳም ለሕዝቦቹ መጠጥን በፈለገ ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ) ፡ ፡ « ድንጋዩንም በበትርህ ምታ » አልነው ፡ ፡ ( መታውም ) ከርሱም ዐሥራሁለት ምንጮች ፈለቁ ፡ ፡ ሰዎቹ ሁሉ መጠጫቸውን በእርግጥ ዐወቁ ፡ ፡ « ከአላህ ሲሳይ ብሉ ፤ ጠጡም ፤ አመጠኞችም ኾናችሁ በምድር ላይ አታበላሹ » ( አልናቸው ) ፡ ፡
(trg)="s2.60.0"> E quando Mosè chiese acqua per il suo popolo , dicemmo : “ Colpisci la roccia con il tuo bastone” .
(trg)="s2.60.1"> E , improvvisamente , sgorgarono dodici fonti , e ogni tribù seppe dove doveva bere !

(src)="s2.61"> ሙሳ ሆይ ፡ - « በአንድ ( ዓይነት ) ምግብ ላይ በፍጹም አንታገሥም ፤ ስለዚህ ጌታህን ከዚያ ምድር ከምታበቅለው ሁሉ ከቅጠላቅጠል ከዱባዋም ከስንዴዋም ከምስርዋም ከሽንኩርቷም ለኛ ያወጣ ዘንድ ለኛ ለምንልን » ባላችሁም ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ፡ ፡ ሙሳም ፡ - « ያንን እርሱ ዝቅተኛ የኾነውን በዚያ እርሱ በላጭ በኾነው ነገር ለውጥን ትፈልጋላችሁን ? ወደ ከተማ ውረዱ ፤ ለናንተም የጠየቃችሁት ነገር አላችሁ » አላቸው ፡ ፡ በነርሱም ላይ ውርደትና ድኽነት ተመታባቸው ፡ ፡ ከአላህም በኾነ ቁጣ ተመለሱ ፡ ፡ ይህ እነርሱ በአላህ ታምራቶች ይክዱና ነቢያትንም ያለ ሕግ ይገድሉ ስለነበሩ ነው ፡ ፡ ይህ በማመጻቸውና ወሰን የሚያልፉ በመኾናቸው ነው ፡ ፡
(trg)="s2.61.3"> Tornate in Egitto , colà troverete certamente quello che chiedete !” .
(trg)="s2.61.4"> E furono colpiti dall' abiezione e dalla miseria e subirono la collera di Allah , perché dissimulavano i segni di Allah e uccidevano i profeti ingiustamente .

(src)="s2.62"> እነዚያ ያመኑ እነዚያም ይሁዳውያን የኾኑ ፣ ክርስቲያኖችም ፣ ሳቢያኖችም ( ከእነርሱ ) በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ለነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው ፡ ፡ በነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም ፤ እነሱም አያዝኑም ፡ ፡
(trg)="s2.62.0"> In verità , coloro che credono , siano essi giudei , nazareni o sabei , tutti coloro che credono in Allah e nell' Ultimo Giorno e compiono il bene riceveranno il compenso presso il loro Signore .
(trg)="s2.62.1"> Non avranno nulla da temere e non saranno afflitti .

(src)="s2.63"> ከበላያችሁም የጡርን ተራራ ያነሳን ኾነን የጠበቀ ቃልኪዳናችሁን በያዝን ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ) ፡ ፡ « ያንን የሰጠናችሁን በኀይል ያዙ ፤ በውስጡ ያለውንም ነገር ( ከእሳት ) ትጠበቁ ዘንድ አስታውሱ » ( አልን ) ፡ ፡
(trg)="s2.63.0"> E quando stringemmo il Patto con voi ed elevammo il Monte : “ Tenetevi saldi a quello che vi abbiamo dato e ricordatevi di quello che contiene !” .
(trg)="s2.63.1"> Forse potrete essere timorati !

(src)="s2.64"> ከዚያም ከዚህ በኋላ ( ኪዳኑን ) ተዋችሁ ፡ ፡ በናንተም ላይ የአላህ ችሮታና እዝነቱ ባልነበረ ኖሮ በእርግጥ ከጠፊዎቹ በኾናችሁ ነበር ፡ ፡
(trg)="s2.64"> Ma poi volgeste le spalle , e senza la grazia di Allah e la Sua misericordia per voi , sareste certamente stati tra i perdenti .

(src)="s2.65"> እነዚያንም ከእናንተ ውስጥ በቅዳሜ ቀን ( ዐሣን በማጥመድ ) ወሰን ያለፉትንና ለነሱ « ወራዳዎች ስትኾኑ ዝንጀሮዎች ኹኑ » ያልናቸውን በእርግጥ ዐወቃችሁ ፡ ፡
(trg)="s2.65"> Avrete saputo di quelli dei vostri che trasgredirono il Sabato ai quali dicemmo : “ Siate scimmie reiette” .

(src)="s2.66"> ( ቅጣቲቱንም ) ለነዚያ በስተፊትዋ ለነበሩትና ለነዚያም ከበኋላዋ ላሉት ( ሕዝቦች ) መቀጣጫ ለፈራህያንም መገሰጫ አደረግናት ፡ ፡
(trg)="s2.66"> Ne facemmo un terribile esempio per i loro contemporanei e per le generazioni che sarebbero seguite e un ammonimento ai timorati .

(src)="s2.67"> ሙሳም ለሕዝቦቹ ፡ - « አላህ ላምን እንድታርዱ ያዛችኋል » ባለ ጊዜ ( አስታወሱ ) ፡ ፡ « መሳለቂያ አድርገህ ትይዘናለህን ? » አሉት ፡ ፡ « ከተሳላቂዎች ከመኾን በአላህ እጠበቃለሁ » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.67.0"> E quando Mosè disse al suo popolo : “ Allah vi ordina di sacrificare una giovenca !” .
(trg)="s2.67.1"> Risposero : “ Ti prendi gioco di noi ?” .

(src)="s2.68"> « ለኛ ጌታህን ጠይቅልን ፤ እርሷ ምን እንደኾነች ( ዕድሜዋን ) ያብራራልን » አሉ ፡ ፡ « እርሱ እርሷ ያላረጀች ጥጃም ያልኾነች በዚህ መካከል ልከኛ የኾነች ጊደር ናት ይላችኋል ፤ የታዘዛችሁትንም ሥሩ » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.68.0"> Dissero : “ Chiedi per noi al tuo Signore che ci indichi come deve essere” .
(trg)="s2.68.1"> Rispose : “ Allah dice che deve essere una giovenca né vecchia , né vergine , ma di età media .

(src)="s2.69"> « ለኛ ጌታህን ጠይቅልን ፤ መልኳ ምን እንደኾነ ለኛ ይግለጽልን » አሉ ፡ ፡ « እርሱ እርሷ መልኳ ደማቅ ተመልካቾችን የምታስደስት ዳለቻ ላም ናት ይላችኋል » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.69.0"> Dissero : “ Chiedi per noi al tuo Signore che ci indichi di che colore deve essere” .
(trg)="s2.69.1"> Rispose : “ Allah dice che dev'essere una giovenca gialla , di un colore vivo che rallegri la vista” .

(src)="s2.70"> « ለኛ ጌታህን ጠይቅልን ፤ እርሷ ምን እንደኾነች ይግለጽልን ፤ ከብቶች በኛ ላይ ተመሳሰሉብን ፡ ፡ እኛም አላህ የሻ እንደኾነ በእርግጥ ተመሪዎች ነን » አሉ ፡ ፡
(trg)="s2.70.0"> Dissero : “ Chiedi al tuo Signore che dia maggiori particolari , perché veramente per noi le giovenche si assomigliano tutte .
(trg)="s2.70.1"> Così , se Allah vuole , saremo ben guidati” .

(src)="s2.71"> « እርሱ እርሷ ያልተገራች ምድርን ( በማረስ ) የማታስነሳ እርሻንም የማታጠጣ ( ከነውር ) የተጠበቀች ልዩ ምልክት የሌለባት ናት ይላችኋል » አላቸው ፡ ፡ « አሁን በትክክል መጣህ » አሉ ፤ ሊሠሩ ያልተቃረቡም ሲኾኑ አረዷት ፡ ፡
(trg)="s2.71.0"> Rispose : “ Egli dice che deve essere una giovenca che non sia stata soggiogata al lavoro dei campi o all' irrigazione , sana e senza difetti” .
(trg)="s2.71.1"> Dissero : “ Ecco , ora ce l' hai descritta esattamente” .

(src)="s2.72"> ነፍስነም በገደላችሁና በርሷም ( ገዳይ ) በተከራከራችሁ ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡ አላህም ትደብቁት የነበራችሁትን ሁሉ ገላጭ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.72.0"> Avevate ucciso un uomo e vi accusavate a vicenda ...
(trg)="s2.72.1"> Ma Allah palesa quello che celate .

(src)="s2.73"> « ( በድኑን ) በከፊሏም ምቱት » አልን ፤ እንደዚሁ አላህ ሙታንን ያስነሳል ፤ ታውቁም ዘንድ ታምራቶችን ያሳያችኋል ፡ ፡
(trg)="s2.73.0"> Allora dicemmo : “ Colpite il cadavere con una parte della giovenca” .
(trg)="s2.73.1"> Così Allah resuscita i morti e vi mostra i Suoi segni affinché possiate comprendere .

(src)="s2.74"> ከዚያም ከዚህ በኋላ ልቦቻችሁ ደረቁ ፤ እርሷም እንደ ድንጋዮች ወይም በድርቅና ይበልጥ የበረታች ናት ፡ ፡ ከድንጋዮችም ከርሱ ጂረቶች የሚፈሱለት አልለ ፡ ፡ ከነርሱም በእርግጥ የሚሰነጠቅና ከርሱ ውሃ ( ምንጭ ) የሚወጣው አልለ ፡ ፡ ከነርሱም አላህን ከመፍራት የተነሳ ወደ ታች የሚወርድ አልለ ፡ ፡ አላህም ከምትሠሩት ነገር ዘንጊ አይደለም ፡ ፡
(trg)="s2.74.0"> Dopo di ciò i vostri cuori si sono induriti ancora una volta , ed essi sono come pietre o ancora più duri .
(trg)="s2.74.1"> Vi sono , infatti , pietre da cui scaturiscono i ruscelli , che si spaccano perché l' acqua fuoriesca , e altre che franano per il timore di Allah .