# am/sadiq.xml.gz
# id/indonesian.xml.gz
(src)="s1.1"> በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው ፡ ፡
(trg)="s1.1"> Dengan menyebut nama Allah Yang Maha Pemurah lagi Maha Penyayang .
(src)="s1.2"> ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው ፤
(trg)="s1.2"> Segala puji bagi Allah , Tuhan semesta alam .
(src)="s1.3"> እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ
(trg)="s1.3"> Maha Pemurah lagi Maha Penyayang .
(src)="s1.4"> የፍርዱ ቀን ባለቤት ለኾነው ፡ ፡
(trg)="s1.4"> Yang menguasai di Hari Pembalasan .
(src)="s1.5"> አንተን ብቻ እንግገዛለን ፤ አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን ፡ ፡
(trg)="s1.5"> Hanya Engkaulah yang kami sembah , dan hanya kepada Engkaulah kami meminta pertolongan .
(src)="s1.6"> ቀጥተኛውን መንገድ ምራን ፡ ፡
(trg)="s1.6"> Tunjukilah kami jalan yang lurus ,
(src)="s1.7"> የእነዚያን በነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን በነሱ ላይ ያልተቆጣህባቸውንና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ( ምራን ፤ በሉ ) ፡ ፡
(trg)="s1.7"> ( yaitu ) Jalan orang-orang yang telah Engkau beri nikmat kepada mereka ; bukan ( jalan ) mereka yang dimurkai dan bukan ( pula jalan ) mereka yang sesat .
(src)="s2.1"> አ.ለ.መ
(trg)="s2.1"> Alif laam miim .
(src)="s2.2"> ይህ መጽሐፍ ( ከአላህ ለመኾኑ ) ጥርጥር የለበትም ፤ ለፈራህያን መሪ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.2"> Kitab ( Al Quran ) ini tidak ada keraguan padanya ; petunjuk bagi mereka yang bertakwa ,
(src)="s2.3"> ለነዚያ በሩቁ ነገር የሚያምኑ ሶላትንም ደንቡን ጠብቀው የሚሰግዱ ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚቸሩ ለኾኑት ፤
(trg)="s2.3"> ( yaitu ) mereka yang beriman kepada yang ghaib , yang mendirikan shalat , dan menafkahkan sebahagian rezeki yang Kami anugerahkan kepada mereka .
(src)="s2.4"> ለእነዚያም ወደ አንተ በተወረደውና ከአንተ በፊትም በተወረደው የሚያምኑ በመጨረሻይቱም ( ዓለም ) እነርሱ የሚያረጋግጡ ለኾኑት ( መሪ ነው ) ፡ ፡
(trg)="s2.4"> dan mereka yang beriman kepada Kitab ( Al Quran ) yang telah diturunkan kepadamu dan Kitab-kitab yang telah diturunkan sebelummu , serta mereka yakin akan adanya ( kehidupan ) akhirat .
(src)="s2.5"> እነዚያ ከጌታቸው በመመራት ላይ ናቸው ፤ እነዚያም እነሱ ፍላጎታቸውን ያገኙ ናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.5"> Mereka itulah yang tetap mendapat petunjuk dari Tuhan mereka , dan merekalah orang-orang yang beruntung .
(src)="s2.6"> እነዚያ የካዱት ( ሰዎች ) ብታስፈራራቸውም ባታስፈራራቸውም በነርሱ ላይ እኩል ነው ፤ አያምኑም ፡ ፡
(trg)="s2.6"> Sesungguhnya orang-orang kafir , sama saja bagi mereka , kamu beri peringatan atau tidak kamu beri peringatan , mereka tidak juga akan beriman .
(src)="s2.7"> አላህ በልቦቻቸው ላይ በመስሚያቸውም ላይ አትሞባቸዋል ፤ በዓይኖቻቸውም ላይ መሸፈኛ አልለ ፤ ለነሱም ታላቅ ቅጣት አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.7.0"> Allah telah mengunci-mati hati dan pendengaran mereka , dan penglihatan mereka ditutup .
(trg)="s2.7.1"> Dan bagi mereka siksa yang amat berat .
(src)="s2.8"> ከሰዎችም « በአላህና በመጨረሻው ቀን አምነናል » የሚሉ አልሉ ፤ እነርሱም አማኞች አይደሉም ፡ ፡
(trg)="s2.8"> Di antara manusia ada yang mengatakan : " Kami beriman kepada Allah dan Hari kemudian , " pada hal mereka itu sesungguhnya bukan orang-orang yang beriman .
(src)="s2.9"> አላህንና እነዚያን ያመኑትን ( ሰዎች ) ያታልላሉ ፤ የማያውቁ ሲኾኑ ነፍሶቻቸውን እንጅ ሌላን አያታልሉም ፡ ፡
(trg)="s2.9"> Mereka hendak menipu Allah dan orang-orang yang beriman , padahal mereka hanya menipu dirinya sendiri sedang mereka tidak sadar .
(src)="s2.10"> በልቦቻቸው ውስጥ ( የንፍቅና ) በሽታ አለባቸው ፡ ፡ አላህም በሽታን ጨመረባቸው ፡ ፡ ለነርሱም ይዋሹ በነበሩት ምክንያት አሳማሚ ቅጣት አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.10"> Dalam hati mereka ada penyakit , lalu ditambah Allah penyakitnya ; dan bagi mereka siksa yang pedih , disebabkan mereka berdusta .
(src)="s2.11"> ለነርሱም « በምድር ላይ አታበላሹ » በተባሉ ጊዜ « እኛ አሳማሪዎች ብቻ ነን » ይላሉ ፡ ፡
(trg)="s2.11.0"> Dan bila dikatakan kepada mereka : " Janganlah kamu membuat kerusakan di muka bumi " .
(trg)="s2.11.1"> Mereka menjawab : " Sesungguhnya kami orang-orang yang mengadakan perbaikan " .
(src)="s2.12"> ንቁ እነርሱ አጥፊዎቹ እነሱው ናቸው ፤ ግን አያውቁም ፡ ፡
(trg)="s2.12"> Ingatlah , sesungguhnya mereka itulah orang-orang yang membuat kerusakan , tetapi mereka tidak sadar .
(src)="s2.13"> ለነሱም « ሰዎቹ እንዳመኑ እመኑ » በተባሉ ጊዜ « ቂሎቹ እንዳመኑ እናምናለን ? » ይላሉ ፡ ፡ አዋጅ ንቁ እነርሱ ቂሎቹ እነርሱው ናቸው ፤ ግን አያውቁም ፡ ፡
(trg)="s2.13.0"> Apabila dikatakan kepada mereka : " Berimanlah kamu sebagaimana orang-orang lain telah beriman " .
(trg)="s2.13.1"> Mereka menjawab : " Akan berimankah kami sebagaimana orang-orang yang bodoh itu telah beriman ? "
(src)="s2.14"> እነዚያንም ያመኑትን በተገናኙ ጊዜ « አምነናል » ይላሉ ፡ ፡ ወደ ሰይጣኖቻቸውም ባገለሉ ጊዜ « እኛ ከናንተ ጋር ነን ፤ እኛ ( በነሱ ) ተሳላቂዎች ብቻ ነን » ይላሉ ፡ ፡
(trg)="s2.14.0"> Dan bila mereka berjumpa dengan orang-orang yang beriman , mereka mengatakan : " Kami telah beriman " .
(trg)="s2.14.1"> Dan bila mereka kembali kepada syaitan-syaitan mereka , mereka mengatakan : " Sesungguhnya kami sependirian dengan kamu , kami hanyalah berolok-olok " .
(src)="s2.15"> አላህ በነሱ ይሳለቅባቸዋል ፤ በጥመታቸውም ውስጥ የሚዋልሉ ሲኾኑ ያዘገያቸዋል ፡ ፡
(trg)="s2.15"> Allah akan ( membalas ) olok-olokan mereka dan membiarkan mereka terombang-ambing dalam kesesatan mereka .
(src)="s2.16"> እነዚህ እነዚያ ስህተትን በቅንነት የገዙ ናቸው ፡ ፡ ንግዳቸውም አላተረፈችም ፤ ቀጥተኞችም አልኾኑም ፡ ፡
(trg)="s2.16"> Mereka itulah orang yang membeli kesesatan dengan petunjuk , maka tidaklah beruntung perniagaan mereka dan tidaklah mereka mendapat petunjuk .
(src)="s2.17"> ( በንፍቅና ) ምሳሌያቸው እንደዚያ እሳትን እንዳነደደ ሰው በዙሪያው ያለውን ሁሉ ባበራች ጊዜም አላህ ብርሃናቸውን እንደወሰደባቸው በጨለማዎችም ውስጥ የማያዩ ኾነው እንደተዋቸው ( ሰዎች ) ብጤ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.17"> Perumpamaan mereka adalah seperti orang yang menyalakan api , maka setelah api itu menerangi sekelilingnya Allah hilangkan cahaya ( yang menyinari ) mereka , dan membiarkan mereka dalam kegelapan , tidak dapat melihat .
(src)="s2.18"> ( እነሱ ) ደንቆሮዎች ፣ ዲዳዎች ፣ ዕውሮች ናቸው ፤ ስለዚህ እነርሱ አይመለሱም ፡ ፡
(trg)="s2.18"> Mereka tuli , bisu dan buta , maka tidaklah mereka akan kembali ( ke jalan yang benar ) ,
(src)="s2.19"> ወይም ( ምሳሌያቸው ) ከሰማይ እንደ ወረደ ዝናም ( ባለቤቶች ) ነው ፤ በርሱ ( በደመናው ) ውስጥ ጨለማዎች ፣ ነጎድጓድም ፣ ብልጭታም ያሉበት ሲኾን ከመብረቆቹ ሞትን ለመፍራት ጣቶቻቸውን በጆሮቻቸው ውስጥ እንደሚያደርጉ ብጤ ነው ፡ ፡ አላህም ከሓዲዎችን ከባቢ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.19.0"> atau seperti ( orang-orang yang ditimpa ) hujan lebat dari langit disertai gelap gulita , guruh dan kilat ; mereka menyumbat telinganya dengan anak jarinya , karena ( mendengar suara ) petir , sebab takut akan mati .
(trg)="s2.19.1"> Dan Allah meliputi orang-orang yang kafir .
(src)="s2.20"> ብልጭታው ዓይኖቻቸውን ሊነጥቅ ይቀርባል ፡ ፡ ለነርሱ ባበራላቸው ቁጥር በርሱ ውስጥ ይኼዳሉ ፡ ፡ በነሱም ላይ ባጨለመ ጊዜ ይቆማሉ ፡ ፡ አላህም በሻ ኖሮ መስሚያቸውንና ማያዎቻቸውን በወሰደ ነበር ፤ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነውና ፡ ፡
(trg)="s2.20.1"> Setiap kali kilat itu menyinari mereka , mereka berjalan di bawah sinar itu , dan bila gelap menimpa mereka , mereka berhenti .
(trg)="s2.20.2"> Jikalau Allah menghendaki , niscaya Dia melenyapkan pendengaran dan penglihatan mereka .
(src)="s2.21"> እናንተ ሰዎች ሆይ ! የፈጠራችሁን እነዚያንም ከናንተ በፊት የነበሩትን ( የፈጠረውን ) ጌታችሁን ተገዙ ፤ ( ቅጣትን ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና ፡ ፡
(trg)="s2.21"> Hai manusia , sembahlah Tuhanmu yang telah menciptakanmu dan orang-orang yang sebelummu , agar kamu bertakwa ,
(src)="s2.22"> ( እርሱ ) ያ ለናንተ ምድርን ምንጣፍ ሰማይንም ጣራ ያደረገ ነው ፤ ከሰማይም ( ከደመና ) ውሃን ያወረደ በርሱም ከፍሬዎች ለናንተ ሲሳይን ያወጣ ነው ፡ ፡ እናንተም ( ፈጣሪነቱን ) የምታውቁ ስትኾኑ ለአላህ ባላንጣዎችን አታድርጉ ፡ ፡
(trg)="s2.22"> Dialah yang menjadikan bumi sebagai hamparan bagimu dan langit sebagai atap , dan Dia menurunkan air ( hujan ) dari langit , lalu Dia menghasilkan dengan hujan itu segala buah-buahan sebagai rezeki untukmu ; karena itu janganlah kamu mengadakan sekutu-sekutu bagi Allah , padahal kamu mengetahui .
(src)="s2.23"> በባሪያችንም ላይ ካወረድነው በመጠራጠር ውስጥ ብትኾኑ ከብጤው አንዲትን ምዕራፍ አምጡ ፡ ፡ እውነተኞችም እንደኾናችሁ ከአላህ ሌላ መስካሪዎቻችሁን ጥሩ ፡ ፡
(trg)="s2.23"> Dan jika kamu ( tetap ) dalam keraguan tentang Al Quran yang Kami wahyukan kepada hamba Kami ( Muhammad ) , buatlah satu surat ( saja ) yang semisal Al Quran itu dan ajaklah penolong-penolongmu selain Allah , jika kamu orang-orang yang benar .
(src)="s2.24"> ( ይህንን ) ባትሠሩ ፈጽሞም አትሠሩትምና ያችን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ድንጋዮች የኾነችውን እሳት ተጠበቁ ፤ ለከሓዲዎች ተደግሳለች ፡ ፡
(trg)="s2.24"> Maka jika kamu tidak dapat membuat ( nya ) -- dan pasti kamu tidak akan dapat membuat ( nya ) , peliharalah dirimu dari neraka yang bahan bakarnya manusia dan batu , yang disediakan bagi orang-orang kafir .
(src)="s2.25"> እነዚያን ያመኑትንና መልካሞችንም የሠሩትን ለነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች ያሏቸው መኾኑን አብስራቸው ፡ ፡ ከርሷ ከፍሬ ( ዓይነት ) ሲሳይን በተመገቡ ቁጥር ( ፍሬዎችዋ ስለሚመሳሰሉ ) « ይህ ያ ከአሁን በፊት የተገመብነው ነው » ይላሉ ፡ ፡ እርሱንም ተመሳሳይ ኾኖ ተሰጡት ፡ ፡ ለነሱም በውስጧ ንጹህ የተደረጉ ሚስቶች አሏቸው ፡ ፡ እነሱም በውስጧ ዘውታሪዎች ናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.25.0"> Dan sampaikanlah berita gembira kepada mereka yang beriman dan berbuat baik , bahwa bagi mereka disediakan surga-surga yang mengalir sungai-sungai di dalamnya .
(trg)="s2.25.1"> Setiap mereka diberi rezeki buah-buahan dalam surga-surga itu , mereka mengatakan : " Inilah yang pernah diberikan kepada kami dahulu " .
(src)="s2.26"> አላህ ማንኛውንም ነገር ትንኝንም ኾነ ( በትንሽነት ወይም በትልቅነት ) ከበላይዋ የኾነንም ምሳሌ ለማድረግ አያፍርም ፡ ፡ እነዚያ ያመኑትማ ፤ እርሱ ( ምሳሌው ) ከጌታቸው ( የተገኘ ) እውነት መኾኑን ያውቃሉ ፡ ፡ እነዚያም የካዱትማ « አላህ በዚህ ምንን ምሳሌ ሻ » ይላሉ ፡ ፡ በርሱ ( በምሳሌው ) ብዙዎችን ያሳስታል በርሱም ብዙዎችን ያቀናል ፡ ፡ በርሱም አመፀኞችን እንጅ ሌላን አያሳስትም ፡ ፡
(trg)="s2.26.1"> Adapun orang-orang yang beriman , maka mereka yakin bahwa perumpamaan itu benar dari Tuhan mereka , tetapi mereka yang kafir mengatakan : " Apakah maksud Allah menjadikan ini untuk perumpamaan ? " .
(trg)="s2.26.2"> Dengan perumpamaan itu banyak orang yang disesatkan Allah , dan dengan perumpamaan itu ( pula ) banyak orang yang diberi-Nya petunjuk .
(src)="s2.27"> እነዚያ የአላህን ቃል ኪዳን ከአጠበቀባቸው በኋላ የሚያፈርሱ እንዲቀጠልም በርሱ ያዘዘውን ነገር የሚቆርጡ በምድርም ላይ የሚያበላሹ እነዚያ እነርሱ ከሳሪዎቹ ናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.27.0"> ( yaitu ) orang-orang yang melanggar perjanjian Allah sesudah perjanjian itu teguh , dan memutuskan apa yang diperintahkan Allah ( kepada mereka ) untuk menghubungkannya dan membuat kerusakan di muka bumi .
(trg)="s2.27.1"> Mereka itulah orang-orang yang rugi .
(src)="s2.28"> ሙታን የነበራችሁ ስትኾኑ ሕያው ያደረጋችሁ ከዚያም የሚገድላችሁ ከዚያም ሕያው የሚያደርጋችሁ ሲኾን ከዚያም ወደርሱ የምትመለሱ ስትኾኑ በአላህ እንዴት ትክዳለችሁ !
(trg)="s2.28"> Mengapa kamu kafir kepada Allah , padahal kamu tadinya mati , lalu Allah menghidupkan kamu , kemudian kamu dimatikan dan dihidupkan-Nya kembali , kemudian kepada-Nya-lah kamu dikembalikan ?
(src)="s2.29"> እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው ፡ ፡ ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ ፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው ፡ ፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.29.0"> Dialah Allah , yang menjadikan segala yang ada di bumi untuk kamu dan Dia berkehendak ( menciptakan ) langit , lalu dijadikan-Nya tujuh langit .
(trg)="s2.29.1"> Dan Dia Maha Mengetahui segala sesuatu .
(src)="s2.30"> ( ሙሐመድ ሆይ ) ጌታህ ለመላእክት ፡ - « እኔ በምድር ላይ ምትክን አድራጊ ነኝ ፤ » ባለ ጊዜ ( የኾነውን አስታውስ ፤ እነርሱም ) « እኛ ከማመስገን ጋር የምናጠራህ ላንተም የምንቀድስ ስንኾን በርሷ ውስጥ የሚያጠፋንና ደሞችንም የሚያፈስን ታደርጋለህን ? » አሉ ፡ ፡ ( አላህ ) « እኔ የማታውቁትን ነገር አውቃለሁ » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.30.0"> Ingatlah ketika Tuhanmu berfirman kepada para Malaikat : " Sesungguhnya Aku hendak menjadikan seorang khalifah di muka bumi " .
(trg)="s2.30.1"> Mereka berkata : " Mengapa Engkau hendak menjadikan ( khalifah ) di bumi itu orang yang akan membuat kerusakan padanya dan menumpahkan darah , padahal kami senantiasa bertasbih dengan memuji Engkau dan mensucikan Engkau ? "
(src)="s2.31"> አደምንም ስሞችን ሁሏንም አስተማረው ፡ ፡ ከዚያም በመላእክት ላይ ( ተጠሪዎቹን ) አቀረባቸው ፡ ፡ « እውነተኞችም እንደኾናችሁ የነዚህን ( ተጠሪዎች ) ስሞች ንገሩኝ » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.31"> Dan Dia mengajarkan kepada Adam nama-nama ( benda-benda ) seluruhnya , kemudian mengemukakannya kepada para Malaikat lalu berfirman : " Sebutkanlah kepada-Ku nama benda-benda itu jika kamu mamang benar orang-orang yang benar ! "
(src)="s2.32"> « ጥራት ይገባህ ፤ ከአስተማርከን ነገር በስተቀር ለኛ ዕውቀት የለንም ፡ ፡ አንተ ዐዋቂው ጥበበኛው አንተ ብቻ ነህና » ( አሉ ) ፡ ፡
(trg)="s2.32"> Mereka menjawab : " Maha Suci Engkau , tidak ada yang kami ketahui selain dari apa yang telah Engkau ajarkan kepada kami ; sesungguhnya Engkaulah Yang Maha Mengetahui lagi Maha Bijaksana " .
(src)="s2.33"> ፡ - « አደም ሆይ ስሞቻቸውን ንገራቸው » አለው ፡ ፡ ስሞቻቸውን በነገራቸውም ጊዜ « እኔ የሰማያትንና የምድርን ሩቅ ምስጢር ዐውቃለሁ ፤ የምትገልጹትንና ያንንም ትደብቁት የነበራችሁትን ዐውቃለሁ አላልኳችሁምን ? » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.33.0"> Allah berfirman : " Hai Adam , beritahukanlah kepada mereka nama-nama benda ini " .
(trg)="s2.33.1"> Maka setelah diberitahukannya kepada mereka nama-nama benda itu , Allah berfirman : " Bukankah sudah Ku-katakan kepadamu , bahwa sesungguhnya Aku mengetahui rahasia langit dan bumi dan mengetahui apa yang kamu lahirkan dan apa yang kamu sembunyikan ? "
(src)="s2.34"> ለመላእክትም « ለአደም ስገዱ » ባልን ጊዜ ( አስታውስ ) ፡ ፡ ሁሉም ወዲያውኑ ሰገዱ ፤ ኢብሊስ ( ዲያብሎስ ) ብቻ ሲቀር እምቢ አለ ፤ ኮራም ከከሓዲዎቹም ኾነ ፡ ፡
(trg)="s2.34"> Dan ( ingatlah ) ketika Kami berfirman kepada para malaikat : " Sujudlah kamu kepada Adam , " maka sujudlah mereka kecuali Iblis ; ia enggan dan takabur dan adalah ia termasuk golongan orang-orang yang kafir .
(src)="s2.35"> « አደም ሆይ ! አንተ ከነሚስትህ በገነት ተቀመጥ ፤ ከርሷም በፈለጋችሁት ስፍራ በሰፊው ተመገቡ ፤ ግን ይህችን ዛፍ አትቅረቡ ፤ ከበደለኞች ትኾናላችሁና » አልንም ፡ ፡
(trg)="s2.35"> Dan Kami berfirman : " Hai Adam , diamilah oleh kamu dan isterimu surga ini , dan makanlah makanan-makanannya yang banyak lagi baik dimana saja yang kamu sukai , dan janganlah kamu dekati pohon ini , yang menyebabkan kamu termasuk orang-orang yang zalim .
(src)="s2.36"> ከርሷም ሰይጣን አዳለጣቸው በውስጡም ከነበሩበት ( ድሎት ) አወጣቸው ፡ ፡ « ከፊላችሁም ለከፊሉ ጠላት ሲኾን ውረዱ ፤ ለናንተም በምድር ላይ እስከ ጊዜ ( ሞታችሁ ) ድረስ መርጊያና መጣቀሚያ አላችሁ » አልናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.36"> Lalu keduanya digelincirkan oleh syaitan dari surga itu dan dikeluarkan dari keadaan semula dan Kami berfirman : " Turunlah kamu ! sebagian kamu menjadi musuh bagi yang lain , dan bagi kamu ada tempat kediaman di bumi , dan kesenangan hidup sampai waktu yang ditentukan " .
(src)="s2.37"> አደምም ከጌታው ቃላትን ተቀበለ ፡ ፡ በርሱ ላይም ( ጌታው ጸጸትን በመቀበል ) ተመለሰለት ፤ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና ፡ ፡
(trg)="s2.37.0"> Kemudian Adam menerima beberapa kalimat dari Tuhannya , maka Allah menerima taubatnya .
(trg)="s2.37.1"> Sesungguhnya Allah Maha Penerima taubat lagi Maha Penyayang .
(src)="s2.38"> « ሁላችሁም ኾናችሁ ከርሷ ውረዱ ፡ ፡ ከኔም የኾነ መመሪያ ቢመጣላችሁ ወዲያውኑ መመሪያዬን የተከተለ ሰው በነሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም ፤ እነሱም አያዝኑም » አልናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.38.0"> Kami berfirman : " Turunlah kamu semuanya dari surga itu !
(trg)="s2.38.1"> Kemudian jika datang petunjuk-Ku kepadamu , maka barang siapa yang mengikuti petunjuk-Ku , niscaya tidak ada kekhawatiran atas mereka , dan tidak ( pula ) mereka bersedih hati " .
(src)="s2.39"> እነዚያም ( በመልክተኞቻችን ) የካዱ በአንቀጾቻችንም ያስተባበሉ እነዚያ የእሳት ጓዶች ናቸው ፡ ፡ እነርሱ በውስጧ ዘውታሪዎች ናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.39"> Adapun orang-orang yang kafir dan mendustakan ayat-ayat Kami , mereka itu penghuni neraka ; mereka kekal di dalamnya .
(src)="s2.40"> የእስራኤል ልጆች ሆይ ! ያችን በናንተ ላይ የለገስኳትን ጸጋዬን አስታውሱ ፡ ፡ በቃል ኪዳኔም ሙሉ ፤ በቃል ኪዳናችሁ እሞላለሁና ፤ እኔንም ብቻ ፍሩ ፡ ፡
(trg)="s2.40"> Hai Bani Israil , ingatlah akan nikmat-Ku yang telah Aku anugerahkan kepadamu , dan penuhilah janjimu kepada-Ku , niscaya Aku penuhi janji-Ku kepadamu ; dan hanya kepada-Ku-lah kamu harus takut ( tunduk ) .
(src)="s2.41"> ከናንተ ጋር ያለውን ( መጽሐፍ ) የሚያረጋግጥ ሆኖ ባወረድኩትም ( ቁርኣን ) እመኑ ፡ ፡ በርሱም የመጀመሪያ ከሓዲ አትሁኑ ፡ ፡ በአንቀጾቼም ጥቂትን ዋጋ አትለውጡ ፡ ፡ እኔንም ብቻ ተጠንቀቁ ፡
(trg)="s2.41"> Dan berimanlah kamu kepada apa yang telah Aku turunkan ( Al Quran ) yang membenarkan apa yang ada padamu ( Taurat ) , dan janganlah kamu menjadi orang yang pertama kafir kepadanya , dan janganlah kamu menukarkan ayat-ayat-Ku dengan harga yang rendah , dan hanya kepada Akulah kamu harus bertakwa .
(src)="s2.42"> እውነቱንም በውሸት አትቀላቅሉ ፡ ፡ እናንተም የምታውቁ ስትሆኑ እውነትን አትደብቁ ፡ ፡
(trg)="s2.42"> Dan janganlah kamu campur adukkan yang hak dengan yang bathil dan janganlah kamu sembunyikan yang hak itu , sedang kamu mengetahui .
(src)="s2.43"> ሶላትንም ደንቡን ጠብቃችሁ ስገዱ ፡ ፡ ዘካንም ( ግዴታ ምጽዋትን ) ስጡ ፡ ፡ ( ለጌታችሁ ) ከአጎንባሾች ጋርም አጎንብሱ ፡ ፡
(trg)="s2.43"> Dan dirikanlah shalat , tunaikanlah zakat dan ruku 'lah beserta orang-orang yang ruku ' .
(src)="s2.44"> እናንተ መጽሐፉን የምታነቡ ሆናችሁ ሰዎችን በበጎ ሥራ ታዛላችሁን ? ነፍሶቻችሁንም ትረሳላችሁን ? ( የሥራችሁን መጥፎነት ) አታውቁምን ?
(trg)="s2.44.0"> Mengapa kamu suruh orang lain ( mengerjakan ) kebaktian , sedang kamu melupakan diri ( kewajiban ) mu sendiri , padahal kamu membaca Al Kitab ( Taurat ) ?
(trg)="s2.44.1"> Maka tidaklah kamu berpikir ?
(src)="s2.45"> በመታገስና በሶላትም ተረዱ ፡ ፡ እርሷም ( ሶላት ) በፈሪዎች ላይ እንጅ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት ፡ ፡
(trg)="s2.45.0"> Jadikanlah sabar dan shalat sebagai penolongmu .
(trg)="s2.45.1"> Dan sesungguhnya yang demikian itu sungguh berat , kecuali bagi orang-orang yang khusyu ' ,
(src)="s2.46"> እነዚያ እነርሱ ጌታቸውን የሚገናኙ እነሱም ወደእርሱ ተመላሾች መኾናቸውን የሚያረጋግጡ በኾኑት ( ላይ እንጅ ከባድ ናት ) ፡ ፡
(trg)="s2.46"> ( yaitu ) orang-orang yang meyakini , bahwa mereka akan menemui Tuhannya , dan bahwa mereka akan kembali kepada-Nya .
(src)="s2.47"> የእስራኤል ልጆች ሆይ ! ያችን በናንተ ላይ የለገስኳትን ጸጋዬንና እኔም በዓለማት ላይ ያበለጥኳችሁ ( አባቶቻችሁን በጊዜያቸው ከነበሩት ዓለማት ያበለጥኩዋቸው ) መኾኔን አስታውሱ ፡ ፡
(trg)="s2.47"> Hai Bani Israil , ingatlah akan nikmat-Ku yang telah Aku anugerahkan kepadamu dan ( ingatlah pula ) bahwasanya Aku telah melebihkan kamu atas segala umat .
(src)="s2.48"> ( ማንኛዋ ) ነፍስም ከ ( ሌላዋ ) ነፍስ ምንንም የማትመነዳበትን ፣ ከርሷም ምልጃን የማይቀበሉባትን ፣ ከርሷም ቤዛ የማይያዝበትን ፣ እነርሱም የማይረዱበትን ቀን ተጠንቀቁ ፡ ፡
(trg)="s2.48"> Dan jagalah dirimu dari ( azab ) hari ( kiamat , yang pada hari itu ) seseorang tidak dapat membela orang lain , walau sedikitpun ; dan ( begitu pula ) tidak diterima syafa 'at dan tebusan dari padanya , dan tidaklah mereka akan ditolong .
(src)="s2.49"> ከፈርዖንም ቤተሰቦች ( ከጎሶቹና ከሰራዊቱ ) ብርቱን ቅጣት የሚያቀምሱዋችሁ ወንዶች ልጆቻችሁን የሚያርዱ ሴቶቻችሁንም የሚተው ሲኾኑ ባዳንናችሁ ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ) ፡ ፡ በዚሃችሁም ከጌታችሁ ታላቅ ፈተና አለበት ፡ ፡
(trg)="s2.49.0"> Dan ( ingatlah ) ketika Kami selamatkan kamu dari ( Fir 'aun ) dan pengikut-pengikutnya ; mereka menimpakan kepadamu siksaan yang seberat-beratnya , mereka menyembelih anak-anakmu yang laki-laki dan membiarkan hidup anak-anakmu yang perempuan .
(trg)="s2.49.1"> Dan pada yang demikian itu terdapat cobaan-cobaan yang besar dari Tuhanmu .
(src)="s2.50"> በናንተም ምክንያት ባሕሩን በከፈልን ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡ ወዲያውም አዳንናችሁ ፡ ፡ የፈርዖንንም ቤተሰቦች እናንተ የምትመለከቱ ኾናችሁ አሰጠምናቸው ፡ ፡
(trg)="s2.50"> Dan ( ingatlah ) , ketika Kami belah laut untukmu , lalu Kami selamatkan kamu dan Kami tenggelamkan ( Fir 'aun ) dan pengikut-pengikutnya sedang kamu sendiri menyaksikan .
(src)="s2.51"> ሙሳንም አርባን ሌሊት በቀጠርነው ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ) ፡ ፡ ከዚያም ከርሱ ( መኼድ ) በኋላ እናንተ በዳዮች ስትኾኑ ወይፈንን ( አምላክ አድርጋችሁ ) ያዛችሁ ፡ ፡
(trg)="s2.51"> Dan ( ingatlah ) , ketika Kami berjanji kepada Musa ( memberikan Taurat , sesudah ) empat puluh malam , lalu kamu menjadikan anak lembu ( sembahan ) sepeninggalnya dan kamu adalah orang-orang yang zalim .
(src)="s2.52"> ከዚያም ከዚህ በኋላ እናንተ ታመሰግኑ ዘንድ ከናንተ ምሕረት አደረግን ፡ ፡
(trg)="s2.52"> Kemudian sesudah itu Kami maafkan kesalahanmu , agar kamu bersyukur .
(src)="s2.53"> ሙሳንም መጽሐፍንና ( እውነትና ውሸትን ) መለያንም ትመሩ ዘንድ በሰጠነው ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡
(trg)="s2.53"> Dan ( ingatlah ) , ketika Kami berikan kepada Musa Al Kitab ( Taurat ) dan keterangan yang membedakan antara yang benar dan yang salah , agar kamu mendapat petunjuk .
(src)="s2.54"> ሙሳም ለሕዝቦቹ ፡ - « ሕዝቦቼ ሆይ ! እናንተ ወይፈንን ( አምላክ አድርጋችሁ ) በመያዛችሁ ነፍሶቻችሁን በደላችሁ ፡ ፡ ወደ ፈጣሪያችሁም ተመለሱ ፤ ነፍሶቻችሁንም ግደሉ ፤ ይሃችሁ በፈጣሪያችሁ ዘንድ ለናንተ በላጭ ነው » ባለ ጊዜ ( አስታውስ ) ፡ ፡ በእናንተም ላይ ጸጸትን በመቀበል ተመለሰላችሁ ፡ ፡ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና ፡ ፡
(trg)="s2.54.0"> Dan ( ingatlah ) , ketika Musa berkata kepada kaumnya : " Hai kaumku , sesungguhnya kamu telah menganiaya dirimu sendiri karena kamu telah menjadikan anak lembu ( sembahanmu ) , maka bertaubatlah kepada Tuhan yang menjadikan kamu dan bunuhlah dirimu .
(trg)="s2.54.1"> Hal itu adalah lebih baik bagimu pada sisi Tuhan yang menjadikan kamu ; maka Allah akan menerima taubatmu .
(src)="s2.55"> « ሙሳ ሆይ ! አላህን በግልጽ እስከምናይ ድረስ ላንተ በፍጹም አናምንልህም » በላችሁም ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡ እናንተም እየተመለከታችሁ መብረቅ ያዘቻችሁ ፡ ፡
(trg)="s2.55"> Dan ( ingatlah ) , ketika kamu berkata : " Hai Musa , kami tidak akan beriman kepadamu sebelum kami melihat Allah dengan terang , karena itu kamu disambar halilintar , sedang kamu menyaksikannya " .
(src)="s2.56"> ከዚያም ታመሰግኑ ዘንድ ከሞታችሁ በኋላ አስነሳናችሁ ፡ ፡
(trg)="s2.56"> Setelah itu Kami bangkitkan kamu sesudah kamu mati , supaya kamu bersyukur .
(src)="s2.57"> በናንተም ላይ ደመናን አጠለልን ፡ ፡ በናተም ላይ ( እንደ ነጭ ማር ያለ ) መንናን እና ድርጭትን አወረድን ፡ ፡ ከሰጠናችሁም ጣፋጮች « ብሉ ( አልን ) ፡ ፡ » አልበደሉንምም ግን ነፍሶቻቸውን ይበድሉ ነበር ፡ ፡
(trg)="s2.57.0"> Dan Kami naungi kamu dengan awan , dan Kami turunkan kepadamu " manna " dan " salwa " .
(trg)="s2.57.1"> Makanlah dari makanan yang baik-baik yang telah Kami berikan kepadamu ; dan tidaklah mereka menganiaya Kami ; akan tetapi merekalah yang menganiaya diri mereka sendiri .
(src)="s2.58"> « ይህችንም ከተማ ግቡ ፡ ፡ ከርሷም በሻችሁት ስፍራ ሰፊን ( ምግብ ) ተመገቡ ፡ ፡ በሩንም ያጎነበሳችሁ ኾናችሁ ግቡ ፤ ( ጥያቄያችን የኃጢአታችን መርገፍ ነው ) በሉም ፡ ፡ ኃጢአቶቻችሁን ለናንተ እንምራለንና ፡ ፡ በጎ ሠሪዎችንም ( ምንዳን ) እንጨምርላቸዋለን » ባልን ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡
(trg)="s2.58"> Dan ( ingatlah ) , ketika Kami berfirman : " Masuklah kamu ke negeri ini ( Baitul Maqdis ) , dan makanlah dari hasil buminya , yang banyak lagi enak dimana yang kamu sukai , dan masukilah pintu gerbangnya sambil bersujud , dan katakanlah : " Bebaskanlah kami dari dosa " , niscaya Kami ampuni kesalahan-kesalahanmu , dan kelak Kami akan menambah ( pemberian Kami ) kepada orang-orang yang berbuat baik " .
(src)="s2.59"> እነዚያም የበደሉት ሰዎች ከዚያ ለነሱ ከተባሉት ሌላ ቃልን ለወጡ ፡ ፡ በነዚያም በበደሉት ላይ ያመጹ በመሆናቸው ምክንያት መቅሠፍትን አወረድንባቸው ፡ ፡
(trg)="s2.59.0"> Lalu orang-orang yang zalim mengganti perintah dengan ( mengerjakan ) yang tidak diperintahkan kepada mereka .
(trg)="s2.59.1"> Sebab itu Kami timpakan atas orang-orang yang zalim itu dari langit , karena mereka berbuat fasik .
(src)="s2.60"> ሙሳም ለሕዝቦቹ መጠጥን በፈለገ ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ) ፡ ፡ « ድንጋዩንም በበትርህ ምታ » አልነው ፡ ፡ ( መታውም ) ከርሱም ዐሥራሁለት ምንጮች ፈለቁ ፡ ፡ ሰዎቹ ሁሉ መጠጫቸውን በእርግጥ ዐወቁ ፡ ፡ « ከአላህ ሲሳይ ብሉ ፤ ጠጡም ፤ አመጠኞችም ኾናችሁ በምድር ላይ አታበላሹ » ( አልናቸው ) ፡ ፡
(trg)="s2.60.2"> Sungguh tiap-tiap suku telah mengetahui tempat minumnya ( masing-masing ) .
(trg)="s2.60.3"> Makan dan minumlah rezeki ( yang diberikan ) Allah , dan janganlah kamu berkeliaran di muka bumi dengan berbuat kerusakan .
(src)="s2.61"> ሙሳ ሆይ ፡ - « በአንድ ( ዓይነት ) ምግብ ላይ በፍጹም አንታገሥም ፤ ስለዚህ ጌታህን ከዚያ ምድር ከምታበቅለው ሁሉ ከቅጠላቅጠል ከዱባዋም ከስንዴዋም ከምስርዋም ከሽንኩርቷም ለኛ ያወጣ ዘንድ ለኛ ለምንልን » ባላችሁም ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ፡ ፡ ሙሳም ፡ - « ያንን እርሱ ዝቅተኛ የኾነውን በዚያ እርሱ በላጭ በኾነው ነገር ለውጥን ትፈልጋላችሁን ? ወደ ከተማ ውረዱ ፤ ለናንተም የጠየቃችሁት ነገር አላችሁ » አላቸው ፡ ፡ በነርሱም ላይ ውርደትና ድኽነት ተመታባቸው ፡ ፡ ከአላህም በኾነ ቁጣ ተመለሱ ፡ ፡ ይህ እነርሱ በአላህ ታምራቶች ይክዱና ነቢያትንም ያለ ሕግ ይገድሉ ስለነበሩ ነው ፡ ፡ ይህ በማመጻቸውና ወሰን የሚያልፉ በመኾናቸው ነው ፡ ፡
(trg)="s2.61.0"> Dan ( ingatlah ) , ketika kamu berkata : " Hai Musa , kami tidak bisa sabar ( tahan ) dengan satu macam makanan saja .
(trg)="s2.61.1"> Sebab itu mohonkanlah untuk kami kepada Tuhanmu , agar Dia mengeluarkan bagi kami dari apa yang ditumbuhkan bumi , yaitu sayur-mayurnya , ketimunnya , bawang putihnya , kacang adasnya , dan bawang merahnya " .
(src)="s2.62"> እነዚያ ያመኑ እነዚያም ይሁዳውያን የኾኑ ፣ ክርስቲያኖችም ፣ ሳቢያኖችም ( ከእነርሱ ) በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ለነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው ፡ ፡ በነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም ፤ እነሱም አያዝኑም ፡ ፡
(trg)="s2.62"> Sesungguhnya orang-orang mukmin , orang-orang Yahudi , orang-orang Nasrani dan orang-orang Shabiin , siapa saja diantara mereka yang benar-benar beriman kepada Allah , hari kemudian dan beramal saleh , mereka akan menerima pahala dari Tuhan mereka , tidak ada kekhawatiran kepada mereka , dan tidak ( pula ) mereka bersedih hati .
(src)="s2.63"> ከበላያችሁም የጡርን ተራራ ያነሳን ኾነን የጠበቀ ቃልኪዳናችሁን በያዝን ጊዜ ( የኾነውን አስታውሱ ) ፡ ፡ « ያንን የሰጠናችሁን በኀይል ያዙ ፤ በውስጡ ያለውንም ነገር ( ከእሳት ) ትጠበቁ ዘንድ አስታውሱ » ( አልን ) ፡ ፡
(trg)="s2.63"> Dan ( ingatlah ) , ketika Kami mengambil janji dari kamu dan Kami angkatkan gunung ( Thursina ) di atasmu ( seraya Kami berfirman ) : " Peganglah teguh-teguh apa yang Kami berikan kepadamu dan ingatlah selalu apa yang ada didalamnya , agar kamu bertakwa " .
(src)="s2.64"> ከዚያም ከዚህ በኋላ ( ኪዳኑን ) ተዋችሁ ፡ ፡ በናንተም ላይ የአላህ ችሮታና እዝነቱ ባልነበረ ኖሮ በእርግጥ ከጠፊዎቹ በኾናችሁ ነበር ፡ ፡
(trg)="s2.64"> Kemudian kamu berpaling setelah ( adanya perjanjian ) itu , maka kalau tidak ada karunia Allah dan rahmat-Nya atasmu , niscaya kamu tergolong orang yang rugi .
(src)="s2.65"> እነዚያንም ከእናንተ ውስጥ በቅዳሜ ቀን ( ዐሣን በማጥመድ ) ወሰን ያለፉትንና ለነሱ « ወራዳዎች ስትኾኑ ዝንጀሮዎች ኹኑ » ያልናቸውን በእርግጥ ዐወቃችሁ ፡ ፡
(trg)="s2.65"> Dan sesungguhnya telah kamu ketahui orang-orang yang melanggar diantaramu pada hari Sabtu , lalu Kami berfirman kepada mereka : " Jadilah kamu kera yang hina " .
(src)="s2.66"> ( ቅጣቲቱንም ) ለነዚያ በስተፊትዋ ለነበሩትና ለነዚያም ከበኋላዋ ላሉት ( ሕዝቦች ) መቀጣጫ ለፈራህያንም መገሰጫ አደረግናት ፡ ፡
(trg)="s2.66"> Maka Kami jadikan yang demikian itu peringatan bagi orang-orang dimasa itu , dan bagi mereka yang datang kemudian , serta menjadi pelajaran bagi orang-orang yang bertakwa .
(src)="s2.67"> ሙሳም ለሕዝቦቹ ፡ - « አላህ ላምን እንድታርዱ ያዛችኋል » ባለ ጊዜ ( አስታወሱ ) ፡ ፡ « መሳለቂያ አድርገህ ትይዘናለህን ? » አሉት ፡ ፡ « ከተሳላቂዎች ከመኾን በአላህ እጠበቃለሁ » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.67.0"> Dan ( ingatlah ) , ketika Musa berkata kepada kaumnya : " Sesungguhnya Allah menyuruh kamu menyembelih seekor sapi betina " .
(trg)="s2.67.1"> Mereka berkata : " Apakah kamu hendak menjadikan kami buah ejekan ? "
(src)="s2.68"> « ለኛ ጌታህን ጠይቅልን ፤ እርሷ ምን እንደኾነች ( ዕድሜዋን ) ያብራራልን » አሉ ፡ ፡ « እርሱ እርሷ ያላረጀች ጥጃም ያልኾነች በዚህ መካከል ልከኛ የኾነች ጊደር ናት ይላችኋል ፤ የታዘዛችሁትንም ሥሩ » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.68.0"> Mereka menjawab : " Mohonkanlah kepada Tuhanmu untuk kami , agar Dia menerangkan kepada kami ; sapi betina apakah itu " .
(trg)="s2.68.1"> Musa menjawab : " Sesungguhnya Allah berfirman bahwa sapi betina itu adalah sapi betina yang tidak tua dan tidak muda ; pertengahan antara itu ; maka kerjakanlah apa yang diperintahkan kepadamu " .
(src)="s2.69"> « ለኛ ጌታህን ጠይቅልን ፤ መልኳ ምን እንደኾነ ለኛ ይግለጽልን » አሉ ፡ ፡ « እርሱ እርሷ መልኳ ደማቅ ተመልካቾችን የምታስደስት ዳለቻ ላም ናት ይላችኋል » አላቸው ፡ ፡
(trg)="s2.69.0"> Mereka berkata : " Mohonkanlah kepada Tuhanmu untuk kami agar Dia menerangkan kepada kami apa warnanya " .
(trg)="s2.69.1"> Musa menjawab : " Sesungguhnya Allah berfirman bahwa sapi betina itu adalah sapi betina yang kuning , yang kuning tua warnanya , lagi menyenangkan orang-orang yang memandangnya " .
(src)="s2.70"> « ለኛ ጌታህን ጠይቅልን ፤ እርሷ ምን እንደኾነች ይግለጽልን ፤ ከብቶች በኛ ላይ ተመሳሰሉብን ፡ ፡ እኛም አላህ የሻ እንደኾነ በእርግጥ ተመሪዎች ነን » አሉ ፡ ፡
(trg)="s2.70"> Mereka berkata : " Mohonkanlah kepada Tuhanmu untuk kami agar Dia menerangkan kepada kami bagaimana hakikat sapi betina itu , karena sesungguhnya sapi itu ( masih ) samar bagi kami dan sesungguhnya kami insya Allah akan mendapat petunjuk ( untuk memperoleh sapi itu ) " .
(src)="s2.71"> « እርሱ እርሷ ያልተገራች ምድርን ( በማረስ ) የማታስነሳ እርሻንም የማታጠጣ ( ከነውር ) የተጠበቀች ልዩ ምልክት የሌለባት ናት ይላችኋል » አላቸው ፡ ፡ « አሁን በትክክል መጣህ » አሉ ፤ ሊሠሩ ያልተቃረቡም ሲኾኑ አረዷት ፡ ፡
(trg)="s2.71.0"> Musa berkata : " Sesungguhnya Allah berfirman bahwa sapi betina itu adalah sapi betina yang belum pernah dipakai untuk membajak tanah dan tidak pula untuk mengairi tanaman , tidak bercacat , tidak ada belangnya " .
(trg)="s2.71.1"> Mereka berkata : " Sekarang barulah kamu menerangkan hakikat sapi betina yang sebenarnya " .
(src)="s2.72"> ነፍስነም በገደላችሁና በርሷም ( ገዳይ ) በተከራከራችሁ ጊዜ ( አስታውሱ ) ፡ ፡ አላህም ትደብቁት የነበራችሁትን ሁሉ ገላጭ ነው ፡ ፡
(trg)="s2.72.0"> Dan ( ingatlah ) , ketika kamu membunuh seorang manusia lalu kamu saling tuduh menuduh tentang itu .
(trg)="s2.72.1"> Dan Allah hendak menyingkapkan apa yang selama ini kamu sembunyikan .
(src)="s2.73"> « ( በድኑን ) በከፊሏም ምቱት » አልን ፤ እንደዚሁ አላህ ሙታንን ያስነሳል ፤ ታውቁም ዘንድ ታምራቶችን ያሳያችኋል ፡ ፡
(trg)="s2.73.0"> Lalu Kami berfirman : " Pukullah mayat itu dengan sebahagian anggota sapi betina itu ! "
(trg)="s2.73.1"> Demikianlah Allah menghidupkan kembali orang-orang yang telah mati , dam memperlihatkan padamu tanda-tanda kekuasaan-Nya agar kamu mengerti .
(src)="s2.74"> ከዚያም ከዚህ በኋላ ልቦቻችሁ ደረቁ ፤ እርሷም እንደ ድንጋዮች ወይም በድርቅና ይበልጥ የበረታች ናት ፡ ፡ ከድንጋዮችም ከርሱ ጂረቶች የሚፈሱለት አልለ ፡ ፡ ከነርሱም በእርግጥ የሚሰነጠቅና ከርሱ ውሃ ( ምንጭ ) የሚወጣው አልለ ፡ ፡ ከነርሱም አላህን ከመፍራት የተነሳ ወደ ታች የሚወርድ አልለ ፡ ፡ አላህም ከምትሠሩት ነገር ዘንጊ አይደለም ፡ ፡
(trg)="s2.74.0"> Kemudian setelah itu hatimu menjadi keras seperti batu , bahkan lebih keras lagi .
(trg)="s2.74.1"> Padahal diantara batu-batu itu sungguh ada yang mengalir sungai-sungai dari padanya dan diantaranya sungguh ada yang terbelah lalu keluarlah mata air dari padanya dan diantaranya sungguh ada yang meluncur jatuh , karena takut kepada Allah .
(src)="s2.75"> ( አይሁዶች ) ከነሱ የኾኑ ጭፍሮች የአላህን ቃል የሚሰሙና ከዚያም ከተረዱት በኋላ እነርሱ እያወቁ የሚለውጡት ሲኾኑ ለናንተ ማመናቸውን ትከጅላላችሁን ?
(trg)="s2.75"> Apakah kamu masih mengharapkan mereka akan percaya kepadamu , padahal segolongan dari mereka mendengar firman Allah , lalu mereka mengubahnya setelah mereka memahaminya , sedang mereka mengetahui ? .